የህብረተሰብ ጤና ቅኝት ሥርዓትና የመረጃ ልዉዉጥ ማጠናከር በማህበረሰብ ላይ ሊከሰት የሚችል ወረርሽኝ ትርጉም ባለዉ መልኩ ለመከላከል ያግዛል – አቶ አንተነህ ፈቃዱ
ሀዋሳ፡ ሚያዝያ 29/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ የህብረተሰብ ጤና ቅኝት ሥርዓትና የመረጃ ልዉዉጥ ማጠናከር በማህበረሰብ ላይ ሊከሰት የሚችል ወረርሽኝ ትርጉም ባለዉ መልኩ ለመከላከል እንደሚያግዝ ገለጹ።
የፌደራልና የክልል ከፍተኛ አመራር አካላትና የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ክልላዊ የህብረተሰብ ጤና ላብራቶሪ ይፋዊ ሥራ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ተካሂዷል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ የህብረተሰብ ጤና ላብራቶሪ ይፋዊ ሥራ ማስጀመሪያ ወቅት እንደተናገሩት፤ የህብረተሰብ ጤና ቅኝት ሥርዓትና የመረጃ ልዉዉጥ ማጠናከር በማህበረሰብ ላይ ሊከሰት የሚችል ወረርሽኝ ትርጉም ባለዉ መልኩ ለመከላከል ያግዛል።
አክለዉም ለተቋሙ ግንባታ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ተቋማት ምስጋና አቅርበዉ በቀጣይ ተቋሙን በማጠናከር ረገድ ድጋፋቸውን እንዲያጠናከሩ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር ዶ/ር ሳሮ አብደላ በበኩላቸው፤ ተቋሙ በአዲስ መልክ በጥራት በተባበረ ደጋፊ በህብረተሰቡ ተሳትፎ መገንባትና ስራ መጀመሩ እጅግ እንደሚያስደስትና በቀጣይ በበለጠ በማደራጀት ሂደት የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቱ ድጋፉ እንደማይለይ ገልፀዋል።
ክልላዊ የህብረተሰብ ጤና ላብራቶሪ ይፋዊ ሥራ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር መድረክ የተለያዩ የመንግስትና ጥሪ የተደረገላቸዉ የህብረተሰብ አካላት በተገኙበት ዉይይት ተካሄዶ ተጠናቋል።
ዘጋቢ፡ ተስፋዬ ወልደማርያም

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ