የህብረተሰብ ጤና ቅኝት ሥርዓትና የመረጃ ልዉዉጥ ማጠናከር በማህበረሰብ ላይ ሊከሰት የሚችል ወረርሽኝ ትርጉም ባለዉ መልኩ ለመከላከል ያግዛል – አቶ አንተነህ ፈቃዱ
ሀዋሳ፡ ሚያዝያ 29/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ የህብረተሰብ ጤና ቅኝት ሥርዓትና የመረጃ ልዉዉጥ ማጠናከር በማህበረሰብ ላይ ሊከሰት የሚችል ወረርሽኝ ትርጉም ባለዉ መልኩ ለመከላከል እንደሚያግዝ ገለጹ።
የፌደራልና የክልል ከፍተኛ አመራር አካላትና የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ክልላዊ የህብረተሰብ ጤና ላብራቶሪ ይፋዊ ሥራ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ተካሂዷል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ የህብረተሰብ ጤና ላብራቶሪ ይፋዊ ሥራ ማስጀመሪያ ወቅት እንደተናገሩት፤ የህብረተሰብ ጤና ቅኝት ሥርዓትና የመረጃ ልዉዉጥ ማጠናከር በማህበረሰብ ላይ ሊከሰት የሚችል ወረርሽኝ ትርጉም ባለዉ መልኩ ለመከላከል ያግዛል።
አክለዉም ለተቋሙ ግንባታ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ተቋማት ምስጋና አቅርበዉ በቀጣይ ተቋሙን በማጠናከር ረገድ ድጋፋቸውን እንዲያጠናከሩ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር ዶ/ር ሳሮ አብደላ በበኩላቸው፤ ተቋሙ በአዲስ መልክ በጥራት በተባበረ ደጋፊ በህብረተሰቡ ተሳትፎ መገንባትና ስራ መጀመሩ እጅግ እንደሚያስደስትና በቀጣይ በበለጠ በማደራጀት ሂደት የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቱ ድጋፉ እንደማይለይ ገልፀዋል።
ክልላዊ የህብረተሰብ ጤና ላብራቶሪ ይፋዊ ሥራ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር መድረክ የተለያዩ የመንግስትና ጥሪ የተደረገላቸዉ የህብረተሰብ አካላት በተገኙበት ዉይይት ተካሄዶ ተጠናቋል።
ዘጋቢ፡ ተስፋዬ ወልደማርያም

More Stories
በክረምት ወራት የሚካሄዱ ስፖርታዊ ውድድሮች ወጣቶች አልባሌ ስፍራ እንዳይውሉ ከማድረግ በተጓዳኝ ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ምቹ እድል እየፈጠረ መሆኑ ተገለጸ
በአርሰናል እንደ አዲስ ብርሃን የፈነጠቀው ክርስቶስ ጾሊስ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጂንካ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለ23ኛ ዙር በተለያዩ የሙያ መስኮች በመደበኛና በማታ መርሃ ግብር ያሰለጠናቸውን 347 ተማሪዎችን አስመረቀ