ሀዋሳ፡ ሚያዝያ 24/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጠቅላይ ሚኒስትር ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረውን የገጠር ኮሪዶር ልማት አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚሰራ የወረዳው አስተዳደር አስታውቋል።
የገጠር ኮሪደር ልማት ስራ ላይ አግኝተን ካነጋገርናቸው አርሶ አደሮች መካከል አቶ አኮ አምባ፣ ገዘኸኝ ገብሬ እና ታደለ ሀደሮ የከጪ ቱታ ቀበሌ ነዋሪዎች ሲሆኑ በተጀመረው የገጠር ኮሪደር ስራ ደስተኞች መሆናቸዉን ተናግረዋል።
አክለውም በአከባቢያቸው የሚገኙ አንደንድ ዘርፈ ብዙ ጥቅም የሌላቸው ዛፎችና ሌሎች ነገሮችን በማንሳት ለኑሮ ምቹ የሆነ አከባቢ ከመፍጠሩም በላይ ልዩ ውበት እየሰጠ መሆኑን ተናግሯል።
የተጀመረው የገጠር ኮሪደር ስራ በተሻለ ጥራት እንዲሠራና በተያዘው ጊዜ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ድርሻ እንሚወጡ ነዋሪዎቹ ገልጿል ።
በወረዳው የተጀመሩ የገጠር ኮሪደር ስራ ለአርሶ አደሮች ኑሮ ምቹ እንደሆነ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሠሩ መሆኑን የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ውለታው ሁሴን ጠቁመው፥ ሌሎች አከባቢዎችን የሚያገናኝ 25 ኪ.ሜ የገጠር ኮሪደር ስራ ለመስራት ቅድመ ሁኔታዎች መጠናቀቃቸውን አስተዳዳሪው አክለው ገልጸዋል።
ዘገቢ፡ አፈወርቅ ኦሹ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ