ሀዋሳ፡ ሚያዝያ 24/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጠቅላይ ሚኒስትር ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረውን የገጠር ኮሪዶር ልማት አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚሰራ የወረዳው አስተዳደር አስታውቋል።
የገጠር ኮሪደር ልማት ስራ ላይ አግኝተን ካነጋገርናቸው አርሶ አደሮች መካከል አቶ አኮ አምባ፣ ገዘኸኝ ገብሬ እና ታደለ ሀደሮ የከጪ ቱታ ቀበሌ ነዋሪዎች ሲሆኑ በተጀመረው የገጠር ኮሪደር ስራ ደስተኞች መሆናቸዉን ተናግረዋል።
አክለውም በአከባቢያቸው የሚገኙ አንደንድ ዘርፈ ብዙ ጥቅም የሌላቸው ዛፎችና ሌሎች ነገሮችን በማንሳት ለኑሮ ምቹ የሆነ አከባቢ ከመፍጠሩም በላይ ልዩ ውበት እየሰጠ መሆኑን ተናግሯል።
የተጀመረው የገጠር ኮሪደር ስራ በተሻለ ጥራት እንዲሠራና በተያዘው ጊዜ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ድርሻ እንሚወጡ ነዋሪዎቹ ገልጿል ።
በወረዳው የተጀመሩ የገጠር ኮሪደር ስራ ለአርሶ አደሮች ኑሮ ምቹ እንደሆነ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሠሩ መሆኑን የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ውለታው ሁሴን ጠቁመው፥ ሌሎች አከባቢዎችን የሚያገናኝ 25 ኪ.ሜ የገጠር ኮሪደር ስራ ለመስራት ቅድመ ሁኔታዎች መጠናቀቃቸውን አስተዳዳሪው አክለው ገልጸዋል።
ዘገቢ፡ አፈወርቅ ኦሹ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ