ሀዋሳ፡ ሚያዝያ 24/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጠቅላይ ሚኒስትር ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረውን የገጠር ኮሪዶር ልማት አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚሰራ የወረዳው አስተዳደር አስታውቋል።
የገጠር ኮሪደር ልማት ስራ ላይ አግኝተን ካነጋገርናቸው አርሶ አደሮች መካከል አቶ አኮ አምባ፣ ገዘኸኝ ገብሬ እና ታደለ ሀደሮ የከጪ ቱታ ቀበሌ ነዋሪዎች ሲሆኑ በተጀመረው የገጠር ኮሪደር ስራ ደስተኞች መሆናቸዉን ተናግረዋል።
አክለውም በአከባቢያቸው የሚገኙ አንደንድ ዘርፈ ብዙ ጥቅም የሌላቸው ዛፎችና ሌሎች ነገሮችን በማንሳት ለኑሮ ምቹ የሆነ አከባቢ ከመፍጠሩም በላይ ልዩ ውበት እየሰጠ መሆኑን ተናግሯል።
የተጀመረው የገጠር ኮሪደር ስራ በተሻለ ጥራት እንዲሠራና በተያዘው ጊዜ እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን ድርሻ እንሚወጡ ነዋሪዎቹ ገልጿል ።
በወረዳው የተጀመሩ የገጠር ኮሪደር ስራ ለአርሶ አደሮች ኑሮ ምቹ እንደሆነ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሠሩ መሆኑን የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ውለታው ሁሴን ጠቁመው፥ ሌሎች አከባቢዎችን የሚያገናኝ 25 ኪ.ሜ የገጠር ኮሪደር ስራ ለመስራት ቅድመ ሁኔታዎች መጠናቀቃቸውን አስተዳዳሪው አክለው ገልጸዋል።
ዘገቢ፡ አፈወርቅ ኦሹ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል