“መጋቢት ሀገራችን ከተጋረጠባት የመበታተን አደጋ የታደገ ወር ነው ” – አቶ ኡስማን ሱሩር
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የዱራሜ ክላስተር ከፍተኛ አመራሮች እና በከምባታ ዞን በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች “ትላንት፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና” በሚል መሪ ቃል የለውጡ አመት የጀመረበትን መጋቢት 24 ሰባተኛ ዓመትን በተለያዩ ሁነቶች እያከበሩ ይገኛሉ።
በመርሃግብሩ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር እንዲሁም የክልሉ የገጠር ክላስተር ከፍተኛ አመራሮችና የከምባታ ዞን የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ባለፉት ሰባት ዓመታት የለውጥ ጊዜያት የተከናወኑ ስራዎች የታሰቡ ሀገራዊ ትልሞችን ያሳካና ቀጣይም የሚያሳካ መሆኑን የተናገሩት የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አረጋ እሸቱ፤ በእነዚህም ዓመታት በርካታ የልማት ትሩፋት የተገኙበት መሆኑን አንስተዋል።
የለውጡ ዓመታት ለኢትዮጵያውያን ብዙ ተስፋ የተጣለበት መሆኑን ያነሱት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር፤ በዚህም በርካታ ፈተናዎች በድል የተቀየሩበት መሆኑንም ገልፀዋል።
መጋቢት ሀገራችን ከተጋረጠባት የመበታተን አደጋ የታደገ፣ የዘመናት የመገፋፋትና የመጠፋፋት የፖለቲካ ባህላችንን ቀይሮ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ እንዲሁም የበለፀገችና የተከበረች ኢትዮጵያን ለትውልድ የማሻገር ህልም የሰነቀ በታላላቅ ስኬቶች የታጀበ ሀገራዊ የለውጥ ጉዞ ዕውን የሆነበት ታሪካዊ ወር መሆኑን አንስተዋል።
የመጣውን ውጤት በጋራ በመስራት ልናዘልቀው ይገባል ሲሉም አቶ ኡስማን ተናግረዋል።
በመድረኩ ባለፉት ሰባት ዓመታት የተገኙ ውጤቶችንና ፈተናዎችን የሚዳስሱ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት እየተደረገባቸው ይገኛል።
ዘጋቢ፡ ቃለአብ ጸጋዬ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል