“ትላንት፣ ዛሬና ነገ ለኢትዮጵያ ልዕልና የመጋቢታውያን የለውጥ ፍሬዎችና የነገ ተስፋዎች” በሚል መሪ ቃል በቡታጅራ ከተማ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ: መጋቢት 24/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ “ትላንት፣ ዛሬና ነገ ለኢትዮጵያ ልዕልና የመጋቢታውያን የለውጥ ፍሬዎችና የነገ ተስፋዎች” በሚል መሪ ቃል የብልፅግና ፓርቲ አመራር እና አባላት የማጠቃለያ የፓናል ውይይት እየተካሄደ ነው።
ባለፉ ሰባት አመታት የተመዘቡ የለውጥ ፍሬዎችን የሚዘከር እና በሚያጋጥሙ አሁናዊ ፈተናዎች ዙሪያ የሚመክር የማጠቃለያ ፓናል ውይይት ‘ትላንት፣ ዛሬና ነገ’ በሚል ርዕስ የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊና የቡታጅራ ክላስተር የብልጽግና ፓርቲ ህብረት ሰብሳቢ አቶ ዳንኤል ዳምጠው የመወያያ ሰነድ አቅርበዋል።
በኢትዮጵያ መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም እውን የሆነውን ሀገራዊ ለውጥ 7ኛ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ አመራር እና አባላት የማጠቃለያ የፓናል ውይይት መካሄድ ጀምሯል ።
በመድረኩ ላይ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማትና ኢንዱስትሪ ክላስተር አስተባባሪና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል፣ ምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፣ የቡታጅራ ከተማ ክላስተር ከፍተኛ አመራሮች፣ ባለሙያዎች ፣ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች እየተሳተፉ ነው፡፡
ዘጋቢ: ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ