“ትላንት፣ ዛሬና ነገ ለኢትዮጵያ ልዕልና የመጋቢታውያን የለውጥ ፍሬዎችና የነገ ተስፋዎች” በሚል መሪ ቃል በቡታጅራ ከተማ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ: መጋቢት 24/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ “ትላንት፣ ዛሬና ነገ ለኢትዮጵያ ልዕልና የመጋቢታውያን የለውጥ ፍሬዎችና የነገ ተስፋዎች” በሚል መሪ ቃል የብልፅግና ፓርቲ አመራር እና አባላት የማጠቃለያ የፓናል ውይይት እየተካሄደ ነው።
ባለፉ ሰባት አመታት የተመዘቡ የለውጥ ፍሬዎችን የሚዘከር እና በሚያጋጥሙ አሁናዊ ፈተናዎች ዙሪያ የሚመክር የማጠቃለያ ፓናል ውይይት ‘ትላንት፣ ዛሬና ነገ’ በሚል ርዕስ የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊና የቡታጅራ ክላስተር የብልጽግና ፓርቲ ህብረት ሰብሳቢ አቶ ዳንኤል ዳምጠው የመወያያ ሰነድ አቅርበዋል።
በኢትዮጵያ መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም እውን የሆነውን ሀገራዊ ለውጥ 7ኛ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ አመራር እና አባላት የማጠቃለያ የፓናል ውይይት መካሄድ ጀምሯል ።
በመድረኩ ላይ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማትና ኢንዱስትሪ ክላስተር አስተባባሪና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል፣ ምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፣ የቡታጅራ ከተማ ክላስተር ከፍተኛ አመራሮች፣ ባለሙያዎች ፣ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች እየተሳተፉ ነው፡፡
ዘጋቢ: ዘላለም ተስፋዬ
More Stories
“ትንንሽ የሚመስሉ ስራዎች ለትልልቅ ዕድሎች በር ይከፍታሉ” – ወይዘሮ ህልውና ጌታቸው
የህግ ታራሚዎችን በስነ ምግባር ለማነፅ በሚደረገው ጥረት ሁሉም ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው የጉራጌ ዞን ፍትህ መምሪያ ገለፀ
የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጆች በክህሎት የበቁ ሥራ ፈጣሪ ዜጎችን ለማፍራት ጥራት ያለውን ስልጠና መስጠታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ተጠቀ