የመጋቢት 24 በዓል በጂንካ ከተማ እየተከበረ ይገኛል
ሀዋሳ፡ መጋቢት 24/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) “ትናንት፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና!” በሚል መሪ ቃል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማህበራዊ ክላስተር ጂንካ ማዕከል፣ ኣሪ ዞን እና ጂንካ ከተማ አስተዳደር የብልጽግና ህብረት አባላት የመጋቢት 24 በዓልን በተለያዩ ዝግጅቶች እያከበሩ ይገኛል።
በአከባበሩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍና የክልሉ የመንግስት ረዳት ተጠሪ ኢንጅነር ፍሬዘር ኮርባይዶ እና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች፣ የኣሪ ዞን እና የጂንካ ከተማ አመራርና ፓርቲ አባላት እየተሣተፉ ይገኛል።
አከባበሩ በፎቶ ኤግዝቢሽንና የጂንካ ከተማ ኮሪደር ልማት ጉብኝት እየተደረገ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ መልካሙ ቡርዝዳቦ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
የሴቶች የልማት ህብረትን በማጠናከር የሴቶችን ተጠቃሚነት በይበልጥ ማረጋገጥ ይገባል – ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
በዞኑ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በግብርናው ዘርፍ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እንደሚሰራ የጋሞ ዞን አሰተዳደር አሰታወቀ
በሀሳብ ልዕልና የሚያምን የፖለቲካ ሥነ-ምህዳርን በማስፋት ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በመመካከርና በመደጋገፍ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ