የመጋቢት 24 በዓል በጂንካ ከተማ እየተከበረ ይገኛል
ሀዋሳ፡ መጋቢት 24/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) “ትናንት፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና!” በሚል መሪ ቃል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማህበራዊ ክላስተር ጂንካ ማዕከል፣ ኣሪ ዞን እና ጂንካ ከተማ አስተዳደር የብልጽግና ህብረት አባላት የመጋቢት 24 በዓልን በተለያዩ ዝግጅቶች እያከበሩ ይገኛል።
በአከባበሩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍና የክልሉ የመንግስት ረዳት ተጠሪ ኢንጅነር ፍሬዘር ኮርባይዶ እና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች፣ የኣሪ ዞን እና የጂንካ ከተማ አመራርና ፓርቲ አባላት እየተሣተፉ ይገኛል።
አከባበሩ በፎቶ ኤግዝቢሽንና የጂንካ ከተማ ኮሪደር ልማት ጉብኝት እየተደረገ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ መልካሙ ቡርዝዳቦ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል