በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ድሬዳዋ ከተማን 4 ለ 1 አሸነፈ፡፡
ለኢትዮጵያ ቡና መስፍን ታፈሰ፣ ሮቤል ተክለሚካኤል፣ አንተነህ ተፈራ እና አማኑኤል ዮሐንስ ጎሎቹን ሲያስቆጥሩ ብቸኛዋን የድሬዳዋ ጎል ያሲን ጀማል አስቆጥሯል፡፡
ኢትዮጵያ ቡና ነጥቡን 30 በማድረስ ከሀድያ ሆሳዕና እና ፋሲል ከነማ ጋር እኩል 5ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል፡፡
ምሽት 12፡00 ላይ ባሕርዳር ከተማ ከኢትዮጵያ መድን ያደረጉት ጨዋታ 2 አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቋል፡፡
የባሕር ዳር ከተማን ጎሎች ሃብታሙ ታደሰ እና አደም አባስ እንዲሁም የኢትዮጵያ መድንን ሳይመን ፒተር እና ሀቢብ ከማል አስቆጥረዋል፡፡

More Stories
አርሰናል በአስቶንቫላ ተሸነፈ
ኮቢ ሜይኑ ማንቸስተር ዩናይትድን መልቀቅ ይፈልጋል
በመላ አፍሪካ ርዕሰ ከተሞች መካከል፣ ለዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲና የጋራ አህጉራዊ ተቋማት ማዕከል በሆነችው ምድራችን፣ ታላቅ የሚዲያ መድረክ ማስተናገድ ታላቅ ኩራት ነው – የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት