በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ድሬዳዋ ከተማን 4 ለ 1 አሸነፈ፡፡
ለኢትዮጵያ ቡና መስፍን ታፈሰ፣ ሮቤል ተክለሚካኤል፣ አንተነህ ተፈራ እና አማኑኤል ዮሐንስ ጎሎቹን ሲያስቆጥሩ ብቸኛዋን የድሬዳዋ ጎል ያሲን ጀማል አስቆጥሯል፡፡
ኢትዮጵያ ቡና ነጥቡን 30 በማድረስ ከሀድያ ሆሳዕና እና ፋሲል ከነማ ጋር እኩል 5ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል፡፡
ምሽት 12፡00 ላይ ባሕርዳር ከተማ ከኢትዮጵያ መድን ያደረጉት ጨዋታ 2 አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቋል፡፡
የባሕር ዳር ከተማን ጎሎች ሃብታሙ ታደሰ እና አደም አባስ እንዲሁም የኢትዮጵያ መድንን ሳይመን ፒተር እና ሀቢብ ከማል አስቆጥረዋል፡፡
More Stories
2ኛው የየም ዞን ስፖርት ሻምፕዮና በሣጃ ከተማ እየተካሄደ ነው
የ2017 የጋሞ ዞን ልዩ ልዩ ስፖርቶች ሻምፒዮና ውድድር በወንዶች እግር ኳስ ውድድር በዳራማሎ ወረዳ አሸናፊነት ተጠናቀቀ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የጅቡቲ አቻውን 6ለ1 አሸነፈ