በዛምቢያ ንዶላ እየተካሄደ ባለው ከ20 ዓመት በታች ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል፡፡
ሁለተኛ ቀኑን ባስቆጠረው ውድድር ዛሬ የ1 ሺህ 500 ሜትር ሴቶች ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተከታትለው በመግባት አሸንፈዋል።
በዚህም አትሌት ውብርስት አስቻለ በአንደኝነት የወርቅ ሜዳሊያ ስታጠልቅ፣ አትሌት ሳምራዊት ሙሉጌታ 2ኛ በመሆን የብር እንዲሁም አትሌት ምጥን እውነቴ በሦስተኝነት የነሐስ ሜዳሊያ አግኝተዋል።
በወንዶች ደግሞ ማሞ ኢማና 2ተኛ ደረጃን በመያዝ ሲያጠናቅቅ ሳሙኤል ቡቼ 4ኛ ገመቹ ቶሎሳ ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል፡፡
በውድድሩ ኢትዮጵያ 2 ወርቅ ፣3 ብር እና 3 ነሃስ በድምሩ 8 ሜዳሊያ ማስመዝገቧን ከኢትጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
More Stories
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል
ስፖርት የወንድማማችነት እና የልማት መጠናከር አንዱ ማሳያ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ አስታወቀ