የዘንድሮ የገና በዓል ገበያ መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ ማሳየቱን የሀዋሳ ከተማ ሸማቾች ተናገሩ
ሀዋሳ፡ ታሕሣሥ 28/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የዘንድሮ የበዓል ገበያ ሁኔታ ከወትሮ ተመጣጣኝ የዋጋ ጭማሪ ማሳየቱን የሀዋሳ ከተማ ሸማቾች ተናግረዋል፡፡
በሀዋሳ ከተማ በተለምዶ አሮጌ ገበያ ተብሎ በሚጠራው የንግድ ማዕከል ተገኝተን ያነጋገርናቸው ሸማቾች በምግብና ምግብ ነክ ሸቀጦች ላይ አንጻራዊ ጭማሪ አለ ብለዋል ፡፡
የበዓል ገበያዉ ካለፉት በዓላት ጋር ሲነፃፀር በተወሰነ ደረጃ ጭማሪ መኖሩን ሸማቾች ገልፀዋል፡፡
የገናን በዓል ምክንያት በማድረግ የዶሮ፣ ቅቤ፣ እንቁላል፣ የቀይ ሽንኩርትና ቅመማቅመሞች ዋጋቸው የጨመረ ሲሆን የነጭ ሽንኩርት ዋጋ እንዳልጨመረ ሸማቾቹ ተናግረዋል፡፡
በተመሳሳይ መልኩ ያነጋገርናቸው ነጋዴዎች በበኩላችው ለዛሬው የበዓል ገበያ ሙሉ ግብአቶችን ይዘው እንደቀረቡ ተናግረው ሕብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ ሁሉም እንደአቅሙ የሚገበያዩበት ሁኔታ እንዳለ ጠቁመዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ሐና በቀለ

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ