የዘንድሮ የገና በዓል ገበያ መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ ማሳየቱን የሀዋሳ ከተማ ሸማቾች ተናገሩ
ሀዋሳ፡ ታሕሣሥ 28/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የዘንድሮ የበዓል ገበያ ሁኔታ ከወትሮ ተመጣጣኝ የዋጋ ጭማሪ ማሳየቱን የሀዋሳ ከተማ ሸማቾች ተናግረዋል፡፡
በሀዋሳ ከተማ በተለምዶ አሮጌ ገበያ ተብሎ በሚጠራው የንግድ ማዕከል ተገኝተን ያነጋገርናቸው ሸማቾች በምግብና ምግብ ነክ ሸቀጦች ላይ አንጻራዊ ጭማሪ አለ ብለዋል ፡፡
የበዓል ገበያዉ ካለፉት በዓላት ጋር ሲነፃፀር በተወሰነ ደረጃ ጭማሪ መኖሩን ሸማቾች ገልፀዋል፡፡
የገናን በዓል ምክንያት በማድረግ የዶሮ፣ ቅቤ፣ እንቁላል፣ የቀይ ሽንኩርትና ቅመማቅመሞች ዋጋቸው የጨመረ ሲሆን የነጭ ሽንኩርት ዋጋ እንዳልጨመረ ሸማቾቹ ተናግረዋል፡፡
በተመሳሳይ መልኩ ያነጋገርናቸው ነጋዴዎች በበኩላችው ለዛሬው የበዓል ገበያ ሙሉ ግብአቶችን ይዘው እንደቀረቡ ተናግረው ሕብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ ሁሉም እንደአቅሙ የሚገበያዩበት ሁኔታ እንዳለ ጠቁመዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ሐና በቀለ

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ