የዘንድሮ የገና በዓል ገበያ መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ ማሳየቱን የሀዋሳ ከተማ ሸማቾች ተናገሩ
ሀዋሳ፡ ታሕሣሥ 28/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የዘንድሮ የበዓል ገበያ ሁኔታ ከወትሮ ተመጣጣኝ የዋጋ ጭማሪ ማሳየቱን የሀዋሳ ከተማ ሸማቾች ተናግረዋል፡፡
በሀዋሳ ከተማ በተለምዶ አሮጌ ገበያ ተብሎ በሚጠራው የንግድ ማዕከል ተገኝተን ያነጋገርናቸው ሸማቾች በምግብና ምግብ ነክ ሸቀጦች ላይ አንጻራዊ ጭማሪ አለ ብለዋል ፡፡
የበዓል ገበያዉ ካለፉት በዓላት ጋር ሲነፃፀር በተወሰነ ደረጃ ጭማሪ መኖሩን ሸማቾች ገልፀዋል፡፡
የገናን በዓል ምክንያት በማድረግ የዶሮ፣ ቅቤ፣ እንቁላል፣ የቀይ ሽንኩርትና ቅመማቅመሞች ዋጋቸው የጨመረ ሲሆን የነጭ ሽንኩርት ዋጋ እንዳልጨመረ ሸማቾቹ ተናግረዋል፡፡
በተመሳሳይ መልኩ ያነጋገርናቸው ነጋዴዎች በበኩላችው ለዛሬው የበዓል ገበያ ሙሉ ግብአቶችን ይዘው እንደቀረቡ ተናግረው ሕብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ ሁሉም እንደአቅሙ የሚገበያዩበት ሁኔታ እንዳለ ጠቁመዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ሐና በቀለ
More Stories
የኣሪ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ባካሄደው 4ኛ ዙር 13ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባኤ ለ2018 በጀት ዓመት ከ2 ቢሊዮን 62 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት አፀደቀ
ለሕዝቡ የሠላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት እንደሚገባ ተገለፀ
በነገው እለት እንደ ሀገር ለሚተከለው የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ ፕሮግራም 1.6 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል መዘጋጀታቸውን የምእራብ ኦሞ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ መልኬ ኬላጌ ተናገሩ