በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ

‎በጎፋ ዞን የዑባ ደብረ ፀሐይ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከመደበኛ የአባላት ወርሃዊ መዋጮ በተጨማሪ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በላይ የዓይነትና የገንዘብ ድጋፍ አድርገዋል።

‎በርክብክብ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የጎፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ቦረና ቦላዶ፤ ፓርቲው ከአባላትና ደጋፊዎች ከ89 ሚሊየን ብር በላይ ለመሰብሰብ አቅዶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረው፤ በዑባ ደብረ ፀሐይ ወረዳ በአይነትና በገንዘብ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በላይ ከሁሉም ቀበሌያት የተሰበሰበውን ሀብት ተረክበዋል።

‎የፓርቲውን አቅም በፋይናንስ መደገፍ ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመፍጠር ወሳኝ በመሆኑ አባላትና ደጋፊዎች ከፓርቲው ጎን መሆን እንዳለባቸው አሳሰበው፤ ለወረዳው የፓርቲ አመራሮችና አባላት በዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ስም ምስጋና አቅርበዋል።

‎የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ መልካሙ ሩንጎ በበኩላቸው፤ ንቅናቄው በ20 ቀበሌያት በከፍተኛ መነሳሳት መከናወኑን ተናግረው በዓይነት 930 ሺህ ብር የሚገመቱ ሰባት ሰንጋ በሬዎች እና 3 ቡሉኮዎች (ባህላዊ አልባሳት) በጥሬ ገንዘብ 255 ሺህ ብር በአጠቃላይ ከ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ሀብት ተሰብሰቦ ማስረከባቸውን ተናግረዋል።

‌‎በቀጣይ እየተሰበሰበ ያለውን ተጨማሪ ሀብት በአጭር ጊዜ ለማሰረከብ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

‎የዑባ ደብረ ፀሐይ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ደመቀች ዝና በበኩላቸው፤ ‎አባላትና ደጋፊዎች ለፓርቲው በአይነትና በገንዘብ ያደረጉት ድጋፍና መነሳሳት የፓርቲውን ህዝባዊ መሰረት ይበልጥ የሚያጠናክር በመሆኑ የሴቶች አባላትና ደጋፊዎች ለፓርቲው አሰፈላጊውን ድጋፍ እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል።

‎ዘጋቢ፡ ስንታየሁ ሙላቱ – ከሰውላ ጣቢያችን