ሀዋሳ፡ ታህሳስ 01/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ለዘመናት የቆየውን የሰላምና የመከባበር ባህል ለማስቀጠል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሚናው ከፍተኛ እንደሆነ ተገልጿል።
በኮሬ ዞን ኬሌ ከተማ አስተዳደር የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ምስረታ ተካሂዷል።
በምስረታው ጉባኤ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በኮሬ ዞን የኬሌ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር ዮሐንስ ኃይሉ እንደተናገሩት፤ ቀጣይነት ያለውን ዕድገትና ሰላም ለማረጋገጥ ከተፈለገ የመከባበር፣ የመቻቻልና የአብሮነት ባህላችንን በማስፋት ልዩነታችንን እያጠበብን መሄድ አለብን።
የሃይማኖት ተቋማት በጋራ ተቀራርበው ከመሥራት ባሻገር በተለያዩ የልማት እንቅስቃሴዎች ላይ በመሳተፍ የራሳቸውን መልካም አሻራ እንዲያሳርፉ ከማድረግ ረገድ የሚመሠረተው ጉባኤ ኃላፊነት እንዳለበት ተናግረዋል።
የኬሌ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ ኢንስፔክተር የጌታነህ ተስፋዬ በበኩላቸው፤ የሃይማኖት ተቋማት ለዘመናት የቆየውን አብሮነት ለማስቀጠልና በመካከላቸው ልዩነቶች እንዳይፈጠሩ ለማድረግ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ሚና ከፍተኛ እንደሆነ ገልጸዋል።
በሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ምስረታ ላይ ለቀጣይ ሁለት ዓመታት የኬሌ ከተማ አስተዳደር ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የሚመሩ ኃላፊዎች ምርጫም ተካሂዷል።
አቶ መሰለ አጋፋሪ እና ቄስ ምህረት ጋሌ የጉባኤው ዋና እና ምክትል ሰብሳቢ ሆነው የተመረጡ ሲሆን በተለይም በእምነት ተቋማት ልዩነቶችና አለመግባባቶች እንዳይፈጠሩ በማድረግ በልማትና በማህበራዊ ሥራዎች ከመንግሥት ጎን በመቆም እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል።
የተሰጠንን ትልቅ ኃላፊነት በጋራ እንድንወጣ ምዕመናን በፀሎትና በሚያስፈልገው ሁሉ ከጎናችን ሊቆሙ ይገባል ብለዋል።
ዘጋቢ፡ ለምለም ኦርሳ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ የአካባቢ ጥበቃን ከማጠናከር ባሻገር የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋምና ለቀጣይ ትውልድ አረንጓዴ አካባቢ ለማውረስ ከፍተኛ ሚና ያለው መሆኑን የኮንታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ገለፁ
ባለፉት 7 አመታት በአንድ ጀምበር ብቻ ከ7 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ በ56 ሚሊዮን የተለያዩ ጠቀሜታዎች ባሏቸዉ ችግኞች መሸፈን መቻላቸዉን የስልጤ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ
በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ቃል የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር እየተካሄደ ይገኛል