19ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀንን አስመልክቶ በዞኑ በሁሉም አቅጣጫዎች ፀጥታን የማስከበር ስራ በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝ የጋሞ ዞን ፖሊስ አስታወቀ
እንግዶች ከበዓሉ ጎን ለጎን ያለ ስጋት የጋሞ ዞን የቱሪስት መዳረሻዎችን እንዲጎበኙም ይደረጋል ተብሏል።
የአርባምንጭ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኢንስፔክተር ጋፋሮ ቶማስ፤ በዓሉን ለማክበር የሚመጡ እንግዶችን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ፖሊስ ጠንካራ የቅድመ ዝግጅት ስራ ማከናወኑን ተናግረዋል።
ከሰላም ወዳዱ የከተማው ህብረተሰብ ጋር ቅንጅታዊ ስራ መሠራቱን ያወሱት ምክትል ኢንስፔክተር ጋፋሮ፤ ህብረተሰቡ ራሱን፣ አካባቢውን እና እንግዶችን እንደሚጠብቅ ክልላዊና ሀገራዊ መድረኮች በአርባምንጭ ከተማ በተካሄዱበት ወቅት በተግባር ማሳየቱን አንስተዋል።
የጋሞ ዞን ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ደበበ ኡንቶ በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል የኢትዮጵያን ህዝቦች የሚያቀራርብ፣ ብዝሃነት የተከበረበትና እኩል ተጠቃሚነት የተረጋገጠበት ቀን መሆኑን አውስተዋል።
በመሆኑም በዞኑ በሚገኙ ሁሉም መዋቅሮችና በአርባምንጭ ከተማ 19ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በደማቅ ሁኔታ እንዲከበር የተለያዩ የዝግጅት ተግባራት ተከናውነዋል ሲሉ አረጋግጠዋል።
በዞኑ በሁሉም አቅጣጫ ፀጥታ የማስከበር ስራ በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዉ፤ ወደ ዞኑ የሚመጡ እንግዶች ያለሥጋት በሁሉም አካባቢዎች መንቀሳቀስ እንዲችሉ ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል።
ዘጋቢ፡ ተመኙህ ገረሱ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

                
                                        
                                        
                                        
                                        
More Stories
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ