ሩድ ቫኔስትሮይ የሌስተር ሲቲ አሰልጣኝ ሆኖ በይፋ ተሾመ
ኔዘርላንዳዊው አሰልጣኝ ሩድ ቫኔስትሮይ የእንግሊዙ ክለብ ሌስተር ሲቲ ዋና አሰልጣኝ በመሆን ተሹሟል።
በቅርቡ ከማንቸስተር ዩናይትድ ግዚያዊ ዋና አሰልጣኝነት የለቀቀው ቫኔስትሮይ በኪንግ ፓወር እንደ አውሮፓውያኑ እስከ 2027 ድረስ የሚያቆየውን ኮንትራት መፈረሙን ክለቡ አሳውቋል።
ሩድ ቫኔስትሮይ ከ5 ቀናት በፊት ከሃላፊነት የተሰናበቱትን ስቲቭ ኩፐርን በመተካት ነው ቀበሮዎችን የተረከበው።
በሌስተር የመጀመሪያ ጨዋታውን የፊታችን ማክሰኞ በኪንግ ፓውር ስታዲየም ከዌስትሃም ዩናይትድ ጋር የሚካሄደውን ጨዋታ በመምራት ይሆናል።
በሙሉቀን ባሳ
More Stories
ሀገር አቀፍ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ያለምንም ችግር እንዲካሄድ በቂ ዝግጅት መደረጉን የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ገለፁ
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል