ሩድ ቫኔስትሮይ የሌስተር ሲቲ አሰልጣኝ ሆኖ በይፋ ተሾመ
ኔዘርላንዳዊው አሰልጣኝ ሩድ ቫኔስትሮይ የእንግሊዙ ክለብ ሌስተር ሲቲ ዋና አሰልጣኝ በመሆን ተሹሟል።
በቅርቡ ከማንቸስተር ዩናይትድ ግዚያዊ ዋና አሰልጣኝነት የለቀቀው ቫኔስትሮይ በኪንግ ፓወር እንደ አውሮፓውያኑ እስከ 2027 ድረስ የሚያቆየውን ኮንትራት መፈረሙን ክለቡ አሳውቋል።
ሩድ ቫኔስትሮይ ከ5 ቀናት በፊት ከሃላፊነት የተሰናበቱትን ስቲቭ ኩፐርን በመተካት ነው ቀበሮዎችን የተረከበው።
በሌስተር የመጀመሪያ ጨዋታውን የፊታችን ማክሰኞ በኪንግ ፓውር ስታዲየም ከዌስትሃም ዩናይትድ ጋር የሚካሄደውን ጨዋታ በመምራት ይሆናል።
በሙሉቀን ባሳ

More Stories
ስፖርት ህዝባዊ መሠራት እንዲኖረው ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ ቀረበ
የጎፋ ዞን የ2018 ዓ.ም ልዩ ልዩ የስፖርት ሻምፒዮና ውድድር እየተካሄደ ነው
በአፍሪካ ዋንጫ የተሳታፊ ሀገራት ቁጥር ላይ ጭማሪ ተደረገ