በ2016 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎች ከ241 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ተግባራት መከናወኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ “በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ቃል ሲካሄድ የቆየው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የማጠቃለያ እና እውቅና መድረክ እየተካሄደ ነወ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቢሮ ኃላፊው አቶ ሉምባ ደምሴ እንደተናገሩት ካለፉት 10 ዓመታት ወዲህ በሀገር አቀፍ ደረጃ መንግስት ለበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ ልዩ ትኩረት ሰጥቷል::
በክልሉም ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር ተጋላጭ ለሆኑ አረጋውያንን፣ አካል ጉዳተኞችን፣ የጎዳና ተዳዳሪዎችን፣ ለጉልበት ብዝበዛ ሰለበ የሆኑ ህፃናትንና ሌሎችን በመደገፍና በመንከባከብ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል::
በ2016 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በ8 ዋና ዋና ተግባራት ከ241 ሚሊየን 33 ሺህ ብር በላይ የሚገመት ተግባራት መከናወኑንም አቶ ሉምባ አመላክተዋል::
በመድረኩም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትልና የማህበራዊ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ሰርካለም ሳሙኤል፤ በ2016 የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማጠቃለያ ሪፖርት እየቀረበ ይገኛል::
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሉምባ ደምሴ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮምቴ ሰብሳቢ አቶ ግዛቸው ዋሌራን ጨምሮ ከሁሉም ዞኖችና ልዩ ወረዳ የመጡ የመምሪያ ኃላፊዎችና በጎ አድራጊዎች እየተሳተፉ ናቸው::
ዘጋቢ: በየነ ሰላሙ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
በሀሬ ተፋሰስበ በ27 ቀናት ወስጥ 35 ሄክታር መሬት ላይ እርከን ፣ አፈር እቀባና የተለያዩ ዕፅዋት ተከላ መከናወኑ ተገለፀ
አዲሱ የቦንጋ ከተማ መዋቅራዊ ፕላን የኡፋ እና የውሽውሽ ከተሞችን ያካተተ መሆኑን በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የከተማ ልማት ዲን አቶ ደጉ በቀለ ገለጹ
የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በየዓመቱ ህዳር 29 ቀን እንዲከበር ሲወሰን ዓላማው ብሔር ብሔረሰቦች ባህሎቻቸውን በመለዋወጥ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጠናከር ሃገራዊ መግባባትን እንዲፈጥሩ ማድረግ ነው – የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር