በ2016 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎች ከ241 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ተግባራት መከናወኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ “በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ቃል ሲካሄድ የቆየው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የማጠቃለያ እና እውቅና መድረክ እየተካሄደ ነወ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቢሮ ኃላፊው አቶ ሉምባ ደምሴ እንደተናገሩት ካለፉት 10 ዓመታት ወዲህ በሀገር አቀፍ ደረጃ መንግስት ለበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ ልዩ ትኩረት ሰጥቷል::
በክልሉም ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር ተጋላጭ ለሆኑ አረጋውያንን፣ አካል ጉዳተኞችን፣ የጎዳና ተዳዳሪዎችን፣ ለጉልበት ብዝበዛ ሰለበ የሆኑ ህፃናትንና ሌሎችን በመደገፍና በመንከባከብ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል::
በ2016 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በ8 ዋና ዋና ተግባራት ከ241 ሚሊየን 33 ሺህ ብር በላይ የሚገመት ተግባራት መከናወኑንም አቶ ሉምባ አመላክተዋል::
በመድረኩም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትልና የማህበራዊ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ሰርካለም ሳሙኤል፤ በ2016 የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማጠቃለያ ሪፖርት እየቀረበ ይገኛል::
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሉምባ ደምሴ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮምቴ ሰብሳቢ አቶ ግዛቸው ዋሌራን ጨምሮ ከሁሉም ዞኖችና ልዩ ወረዳ የመጡ የመምሪያ ኃላፊዎችና በጎ አድራጊዎች እየተሳተፉ ናቸው::
ዘጋቢ: በየነ ሰላሙ – ከሆሳዕና ጣቢያችን
More Stories
በከተማው የሚሰሩ ፕሮጀክቶችን ዕውን ለማድረግ የተሰበሰበውን ሀብት በቁጠባና በግልጸኝነት መጠቀም እንደሚገባ ተገለጸ
ኮሌጆች በዕውቀትና ክህሎት የበለፀገ ትውልድ በማፍራት ችግር ፈቺ የሆኑ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በማበርከት የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተገለፀ
በጎፋ ዞን ኢሲፔ ዲቻ ኃላፊነቱ የተወሰነ የገበሬዎች ሁለገብ ህብረት ሥራ ዩኒየን ካፒታሉን 62 ሚሊየን ብር በማድረስ ዓመታዊ ትርፉ ከ3 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ መሆኑን አስታወቀ