በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎች ድጋፍ አሰጣጥና አስተዳደር ዙሪያ ለዞንና ልዩ ወረዳ አመራሮች እንዲሁም ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በወልቂጤ ከተማ ስልጠና እየተሰጠ ነው።
ስልጠናው የሚሰጠው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ከኢንተርፕሪነር ልማት ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ሲሆን ለሶስት ተከታታይ ቀናት እንደሚቆይ ተጠቁሟል።
በመርሃ ግብሩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ሙዲን ሁሴን፤ የሳይንስና ፈጠራ ስራዎችን በአግባቡ በማልማትና በማስፋት እንደሀገር አለም አቀፍ ተወዳዳሪ መሆን ያስፈልጋል ብለዋል።
የፐብሊክ ኢንተርፕሪነርሺፕና ኢኖቬሽን ኢኮሲስተም እንዲሁም በሳይንስና ቴክኖሎጂ የፈጠራ ስራዎች በማጠናከር የዘርፉን አቅም በማሳደግ ጥራት ያለው አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ ተናግረዋል።
ስልጠናው የሳይንስ ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ አቅም በማሳደግ ረገድ ሚናው ከፍተኛ መሆኑንም ገልፀዋል።
ዘጋቢ፡ አዱኛ ትዕዛዙ – ከወልቂጤ ጣቢያችን
More Stories
አካል ጉዳተኞች መብቶቻቸውና ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ በቅንጅትና በጥምረት መስራት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለፀ
አካባቢን በመጠበቅና በማጽዳት ምቹና ጽዱ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ሁሉም የድርሻውን ልወጣ እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ
ግለሰባዊ ነጠላ ትርክቶችን በጋራ በመታገል በመደመር እሳቤ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ ተገለጸ