በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎች ድጋፍ አሰጣጥና አስተዳደር ዙሪያ ለዞንና ልዩ ወረዳ አመራሮች እንዲሁም ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በወልቂጤ ከተማ ስልጠና እየተሰጠ ነው።
ስልጠናው የሚሰጠው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ከኢንተርፕሪነር ልማት ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ሲሆን ለሶስት ተከታታይ ቀናት እንደሚቆይ ተጠቁሟል።
በመርሃ ግብሩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ሙዲን ሁሴን፤ የሳይንስና ፈጠራ ስራዎችን በአግባቡ በማልማትና በማስፋት እንደሀገር አለም አቀፍ ተወዳዳሪ መሆን ያስፈልጋል ብለዋል።
የፐብሊክ ኢንተርፕሪነርሺፕና ኢኖቬሽን ኢኮሲስተም እንዲሁም በሳይንስና ቴክኖሎጂ የፈጠራ ስራዎች በማጠናከር የዘርፉን አቅም በማሳደግ ጥራት ያለው አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ ተናግረዋል።
ስልጠናው የሳይንስ ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ አቅም በማሳደግ ረገድ ሚናው ከፍተኛ መሆኑንም ገልፀዋል።
ዘጋቢ፡ አዱኛ ትዕዛዙ – ከወልቂጤ ጣቢያችን
More Stories
በኢንቨስትመንት ስም መሬት ወስደው ወደስራ ባልገቡ ባለሀብቶች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ የከተማው አስተዳደር አስታወቀ
በፍየልና በግ ማሞከት ተግባራት ላይ በመሰማራታቸው ተጠቃሚ መሆናቸውን በሀዲያ ዞን አንዳንድ የሶሮ ወረዳ ሴቶች ተናገሩ
የገጠር ተደራሽ መንገድ የበርካቶችን የትራንስፖርት አገልግሎት ችግር እየፈታ መሆኑ ተገለጸ