በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎች ድጋፍ አሰጣጥና አስተዳደር ዙሪያ ለዞንና ልዩ ወረዳ አመራሮች እንዲሁም ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በወልቂጤ ከተማ ስልጠና እየተሰጠ ነው።
ስልጠናው የሚሰጠው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ከኢንተርፕሪነር ልማት ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ሲሆን ለሶስት ተከታታይ ቀናት እንደሚቆይ ተጠቁሟል።
በመርሃ ግብሩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ሙዲን ሁሴን፤ የሳይንስና ፈጠራ ስራዎችን በአግባቡ በማልማትና በማስፋት እንደሀገር አለም አቀፍ ተወዳዳሪ መሆን ያስፈልጋል ብለዋል።
የፐብሊክ ኢንተርፕሪነርሺፕና ኢኖቬሽን ኢኮሲስተም እንዲሁም በሳይንስና ቴክኖሎጂ የፈጠራ ስራዎች በማጠናከር የዘርፉን አቅም በማሳደግ ጥራት ያለው አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ ተናግረዋል።
ስልጠናው የሳይንስ ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ አቅም በማሳደግ ረገድ ሚናው ከፍተኛ መሆኑንም ገልፀዋል።
ዘጋቢ፡ አዱኛ ትዕዛዙ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ