በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎች ድጋፍ አሰጣጥና አስተዳደር ዙሪያ ለዞንና ልዩ ወረዳ አመራሮች እንዲሁም ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በወልቂጤ ከተማ ስልጠና እየተሰጠ ነው።
ስልጠናው የሚሰጠው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ከኢንተርፕሪነር ልማት ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ሲሆን ለሶስት ተከታታይ ቀናት እንደሚቆይ ተጠቁሟል።
በመርሃ ግብሩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ሙዲን ሁሴን፤ የሳይንስና ፈጠራ ስራዎችን በአግባቡ በማልማትና በማስፋት እንደሀገር አለም አቀፍ ተወዳዳሪ መሆን ያስፈልጋል ብለዋል።
የፐብሊክ ኢንተርፕሪነርሺፕና ኢኖቬሽን ኢኮሲስተም እንዲሁም በሳይንስና ቴክኖሎጂ የፈጠራ ስራዎች በማጠናከር የዘርፉን አቅም በማሳደግ ጥራት ያለው አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ ተናግረዋል።
ስልጠናው የሳይንስ ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ አቅም በማሳደግ ረገድ ሚናው ከፍተኛ መሆኑንም ገልፀዋል።
ዘጋቢ፡ አዱኛ ትዕዛዙ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ግማሽ አመት አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በዱራሜ ከተማ እየተካሄደ ነው
መጪው ጠቅላላ ምርጫ ተአማኒና በህዝቡ ዘንድ ቅቡልነት ያለው እንዲሆን በልዩ ትኩረት እንደሚሠራ የባስኬቶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሳሙኤል ደሣለኝ ገለፁ
የጌዴኦ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 28ኛ መደበኛ ጉባኤውን አካሂዷል