አሳሳቢ እየሆነ የመጣውን ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ለመግታት ያስችላል የተባለ ውይይት እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ሕዳር 03/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) አሳሳቢ እየሆነ የመጣውን ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ለመግታት ያስችላል የተባለ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ አዘጋጅነት እየተካሄደ ባለው ውይይት የክልልና የፌደራል የዘርፉ አካላት እየተሳተፋ ነው።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ ሀላፊ አቶ አክመል አህመዲን፤ ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል የህግ ስርዓት ቢዘረጋም የዜጎች ሞት፣ እንግልትና ጥቃት አሁንም አልቆመም ብለዋል።
ችግሩ ዓለም አቀፋዊ በመሆኑ ድንበር ዘለል ትብብርን ይጠይቃል ያሉት ሀላፊው፤ አዋጆችን በወጉ መተግበርና የግንዛቤ ፈጠራ ስራው ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።
የተሻለ ገቢ ፍለጋ እና የህገ ወጥ ደላሎች ተፅዕኖ ዜጎችን ለእንግልት እየዳረገ ነው ያሉት አቶ አክመል፤ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የችግሩ ገፈት ቀማሽ በመሆኑ የጠነከረ የትብብር ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በኢፌዲሪ የፍትህ ሚኒስቴር የፍልሰት ትብብር ጥምረት ጽ/ቤት ዐቃቤ ህግ የሆኑት አቶ ዮሀንስ ሲሳይ በበኩላቸው፤ ችግሩን ለመከላከል የወጡ ህጎችን በወጉ መተግበር ያስፈልጋል ብለዋል።
ዘጋቢ፡ ባየ በልስቲ

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ