አሳሳቢ እየሆነ የመጣውን ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ለመግታት ያስችላል የተባለ ውይይት እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ሕዳር 03/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) አሳሳቢ እየሆነ የመጣውን ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ለመግታት ያስችላል የተባለ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ አዘጋጅነት እየተካሄደ ባለው ውይይት የክልልና የፌደራል የዘርፉ አካላት እየተሳተፋ ነው።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ ሀላፊ አቶ አክመል አህመዲን፤ ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል የህግ ስርዓት ቢዘረጋም የዜጎች ሞት፣ እንግልትና ጥቃት አሁንም አልቆመም ብለዋል።
ችግሩ ዓለም አቀፋዊ በመሆኑ ድንበር ዘለል ትብብርን ይጠይቃል ያሉት ሀላፊው፤ አዋጆችን በወጉ መተግበርና የግንዛቤ ፈጠራ ስራው ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።
የተሻለ ገቢ ፍለጋ እና የህገ ወጥ ደላሎች ተፅዕኖ ዜጎችን ለእንግልት እየዳረገ ነው ያሉት አቶ አክመል፤ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የችግሩ ገፈት ቀማሽ በመሆኑ የጠነከረ የትብብር ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በኢፌዲሪ የፍትህ ሚኒስቴር የፍልሰት ትብብር ጥምረት ጽ/ቤት ዐቃቤ ህግ የሆኑት አቶ ዮሀንስ ሲሳይ በበኩላቸው፤ ችግሩን ለመከላከል የወጡ ህጎችን በወጉ መተግበር ያስፈልጋል ብለዋል።
ዘጋቢ፡ ባየ በልስቲ

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ