ማንቸስተር ዩናይትድ እና ኒውካስል ተጋጣሚዎቻቸውን ሲረቱ ቶትንሃም ተሸነፈ
ሀዋሳ፡ ሕዳር 01/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በ11ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ማንቸስተር ዩናይትድ እና ኒውካስል ተጋጣሚዎቻቸውን ሲያሸንፉ በቶትንሃም በኢፕስዊች ታውን ተረቷል።
በሜዳው ሌስተር ሲቲን ያስተናገደው ማንቸስተር ዩናይትድ 3ለ0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
የማንቸስተር ዩናይትድን የማሸነፊያ ግቦች ብሩኖ ፈርናንዴዝ፣ ቪክቶር ክርስቲያንሰን እና አሌሃንድሮ ጋርናቾ ከመረብ አሳርፈዋል።
በሲቲ ግራውንድ ኖቲንግሃም ፎረስትን የገጠመው ኒውካስል 3ለ1 አሸንፏል።
አሌክሳንደር አይሳክ፣ ጆይሊንተን እና ሃርቬ ባርንስ የኒውካስልን የድል ግቦች ከመረብ ሲያሳርፉ ሙሪሎ ለኖቲንግሃም ፎረስት የማስተዛዘኛዋን ግብ አስቆጥሯል።
ቶትንሃም በበኩሉ አዲስ አዳጊውን ኢፕስዊች ታውንን በሜዳው አስተናግዶ 2ለ1 ተረቷል።
ፕሪሚዬር ሊጉ መካሄዱን ሲቀጥል ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ተጠባቂው የለንደን ደርቢ በቼልሲ እና አርሰናል መካከል በስታንፎርድ ብሪጅ ይካሄዳል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
ሀገር አቀፍ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ያለምንም ችግር እንዲካሄድ በቂ ዝግጅት መደረጉን የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ገለፁ
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል