ማንቸስተር ዩናይትድ እና ኒውካስል ተጋጣሚዎቻቸውን ሲረቱ ቶትንሃም ተሸነፈ
ሀዋሳ፡ ሕዳር 01/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በ11ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ማንቸስተር ዩናይትድ እና ኒውካስል ተጋጣሚዎቻቸውን ሲያሸንፉ በቶትንሃም በኢፕስዊች ታውን ተረቷል።
በሜዳው ሌስተር ሲቲን ያስተናገደው ማንቸስተር ዩናይትድ 3ለ0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
የማንቸስተር ዩናይትድን የማሸነፊያ ግቦች ብሩኖ ፈርናንዴዝ፣ ቪክቶር ክርስቲያንሰን እና አሌሃንድሮ ጋርናቾ ከመረብ አሳርፈዋል።
በሲቲ ግራውንድ ኖቲንግሃም ፎረስትን የገጠመው ኒውካስል 3ለ1 አሸንፏል።
አሌክሳንደር አይሳክ፣ ጆይሊንተን እና ሃርቬ ባርንስ የኒውካስልን የድል ግቦች ከመረብ ሲያሳርፉ ሙሪሎ ለኖቲንግሃም ፎረስት የማስተዛዘኛዋን ግብ አስቆጥሯል።
ቶትንሃም በበኩሉ አዲስ አዳጊውን ኢፕስዊች ታውንን በሜዳው አስተናግዶ 2ለ1 ተረቷል።
ፕሪሚዬር ሊጉ መካሄዱን ሲቀጥል ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ተጠባቂው የለንደን ደርቢ በቼልሲ እና አርሰናል መካከል በስታንፎርድ ብሪጅ ይካሄዳል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
አርሰናል በአስቶንቫላ ተሸነፈ
ኮቢ ሜይኑ ማንቸስተር ዩናይትድን መልቀቅ ይፈልጋል
በመላ አፍሪካ ርዕሰ ከተሞች መካከል፣ ለዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲና የጋራ አህጉራዊ ተቋማት ማዕከል በሆነችው ምድራችን፣ ታላቅ የሚዲያ መድረክ ማስተናገድ ታላቅ ኩራት ነው – የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት