በከተሞች የሚስተዋለውን ህገ-ወጥ አሰራር በመከላከል ፕላንን መሠረት ያደረገ ዕድገት እንዲኖር በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ
ሀዋሳ፡ ጥቅምት 11/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በከተሞች የሚስተዋለውን ህገ-ወጥ አሰራር በመከላከል ፕላንን መሠረት ያደረገ ዕድገት እንዲኖር በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ቢሮ ኃላፊ አቶ ገብረመስቀል ጫላ ተናገሩ።
በከተሞች የሚስተዋለውን ህገ-ወጥ ግንባታና የመሬት ወረራን ለመከላከልና ህጋዊ ስርዓት ለማስያዝ የሚያስችል ምክክር በአርባምንጭ ከተማ ተደርጓል።
የመሬት ወረራን በተደራጀ መልኩ ስርዓት በማስያዝ የከተሞችን ማዘመን እንደሚገባ ያወሱት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ቢሮ ኃላፊ አቶ ገብረመስቀል ጫላ ናቸው።
አሰራር በትክክል መሬት ላይ መውረዱን መከታተል እና የመሬት ወረራ እንዳይፈጸም ቁጥጥር ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
የከተማ መስፋፋት ለአርሶ አደሩ ስጋት መሆን የለበትም ያሉት አቶ ገብረመስቀል መሬትን ከደላላው ነፃ በማውጣት ለሁለንተናዊ ለውጥ ልንጠቀምበት ይገባል ብለዋል።
በከተሞች የገቢ አሰባሰብ ስርዓቱን በማዘመን ከተሞች በገቢ ራሳቸውን እንዲችሉ ማድረግ እንደሚገባ ገልፀው ለመንግስት ሰራተኞችም ቦታ በማዘጋጀት የቤት ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ዘውዴ በበኩላቸው በከተሞች የሚታዩ ችግሮችን መቆጣጠር አለመቻል እና ተንከባለው የመጡ ውስብስብ ችግሮችን አለመቆጣጠር ለከተሞች እድገት እንቅፋት መፍጠሩን ገልፀዋል።
የሚስተዋሉ የህግ ክፍተቶችን በአዲሱ የሊዝ አዋጅ መሰረት መፍታት ያሻል ያሉት አቶ ብርሃኑ፤ የወል መሬቶችን ከመቆጣጠር፣ ሸንሽኖ መሸጥና የመሬት አዋጅን መሰረት ያደረገ አሰራርን ከማስፈን አንፃር ችግሮች ይስተዋላሉ ብለዋል።
ችግሮችን ፈጥነን በመፍታት የከተሞችን ቅርፅ በማስተካከል የከተሞችን እድገት ለማፋጠን መስራት አለብንም ብለዋል አቶ ብርሃኑ።
የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው የመሬት ወረራ ችግርን በመከላከል ረገድ ህገ-ወጥ ደላሎች የህግ የበላይነትን ለማስከበር ለሚደረገው ጥረት እንቅፋት መፍጠራቸውን ነው ያመላከቱት።
ዘጋቢ፡ ተመኙህ ገረሱ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

                
                                        
                                        
                                        
                                        
More Stories
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ