ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የኬሌ ከተማ ዋና አፈጉባኤ ወ/ሮ ሀና ኃይሌ ምክር ቤቱን የመልካም አስተዳደር፣ የግልፀኝነትና ተጠያቂነት እሴቶች ማፍለቂያ ተቋም ለማድረግ ሁሉም ድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል።
የምክር ቤቱ ምክትል አፈጉባዔ አቶ ምናሉ እንዳለ የ2016 በጀት ዓመት የመሥሪያ ቤቶችን አፈፃፀም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆኑ አብዛኛው የተሻለ ሆኖ ሳለ የመስክ ምልከታ፣የተሽከርካሪ እጥረት የፎቶ ኮፒ ማሽን እጥረትና ሌሎችም በደካማ ጎን ተገምግሟል።
የኬሌ ከተማ ከንቲባ ኢንጂነር ዮሐንስ ኃይሉ የከተማው ፈርጅ ለውጥ ለማድረግ የተሠራው ሥራ ተስፋ ሰጪ መሆኑን ገልጸው ለህብረተሰቡ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ አንስተዋል፡፡
ከተሳታፊዎች መካካል የኮሬ ዞን ምክር ቤት አፈጉባዔ ወይዘሮ አካላት በቀለና አቶ ኦላይሴ ኦያደ በኢንተርፕራይዝ፣ በገቢ አሰባሰብና ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለማሻሻል በትኩረት እንዲሠሩ አስተያየት ሰጥተዋል።
ከቋሚ ኮሚቴዎች አቶ ፍራንካ ፍላቴና አቶ ቴወድሮስ ጭርጋ በጀት እንደጸደቀ ወደ ተግባር ያለመግባት ችግሮች መኖሩን አይተው አቅጣጫ ማስቀመጣቸውን ነው የተናገሩት።
የ2017 ዓመት የከተማው በጀት ከመንግሥት ግምጃ ቤት 77 ሚሊየን 979 ሺህ 210፣ ከውስጥ ገቢ 70 ሚሊዮን 654 ሺህ 47 ብር ጠቅላላ 148 ሚሊዮን 633 ሺህ 257 ብር መሆኑ ተገልጿል።
ዘጋቢ፡ ምርጫ መላኩ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
በእንስሳት እርባታ ከተሰማራን ወዲህ ኑሯችን ተሻሽሏል – የጋዘር ከተማ ወጣቶች
በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄን ባህል በማድረግ የአካባቢ ጥበቃ ስራን ማጎልበት ይገባል ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የብሔረሰቦች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አሳሰቡ
ፈጣንና ቀልጣፋ መረጃን ተጀራሽ በማድረግ የመንግስትና የማህበረሰቡን ተግባቦት ይበልጥ ለማጠናከር የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሚና የጎላ መሆኑ ተጠቆመ