በከተማው ካነጋገርናቸው ሴቶች መካከል ወ/ሮ እጅጋየሁ ይማምና ብርቱካን አወቀ እንደተናገሩት በተለይም የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ ብሎም የራሳቸውንና የልጆቻቸውን ጤና ለመጠበቅ በልማት ሕብረት ተደራጅተው በመስራት ውጤታማ መሆን መቻላቸውን ነው የገለጹት።
ቀደም ሲል ከነበረባቸውን የጠባቂነትና የተረጅነት ስሜት በመላቀቅና በሌማት ትሩፋት ዘርፍ በትጋት ሠርተው ኢኮኖሚያቸውን ማሳደግ መቻላቸውን ጠቁመዋል።
በልማቱ ተሳታፊና ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ በትኩረት በመስራት የጓሮ አትክልቶችን ካሮት፣ ሰላጣ፣ ቀይሰር፣ አበባ ጓመንና የመሳሰሉትን በማልማት ተጠቃሚ የሆኑ ሴቶች ለቀጣይም ተለዋጭ ቦታቸውን ለማልማት ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን አስረድተዋል።
የይርጋጨፌ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፖርቲ ጽህፈት ቤት የሴቶች ሊግ ሀላፊ ወ/ሮ አማረች ኦብሴ በ2016 ዓ.ም ከ800 በላይ ሴቶች ወደ ስራ መግባታቸውንና ውጤታማ መሆናቸውን አመላክተዋል።
በተለይም ከተማ አሰተዳደሩ ለችግኝ ግዥ 250 ሺህ ብር ድጋፍ በማድረጉና ቦታ በማዘጋጀቱ ሴቶች ‹‹ምግቤን ከጓሮዬ ጤናዬን ከደጄ›› በሚል ከምግብነትም አልፎ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን አስረድተዋል።
የይርጋጨፌ ከተማ ሴቶችና ህፃናት ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ውቢት ደንቢ ሴቶቸ ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየሰሩ መሆናቸውንና በቀጣይም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አመላክተዋል።
ዘጋቢ ፡ ጽጌ ደምሴ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
“አንድነታችንን በማጎልበት የህዝብ ጥቅም የሚያስቀድም ፖለቲካ ማራመድ ይጠበቅብናል” ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
የሕብረ-ብሔራዊ አንድነት መጠናከር መሰረት የሆነው ብዝሃነትን በአግባቡ የማስተናገድ ሂደት ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያለው መሆኑ ተገለፀ
በክረምቱ ወራት ሊከሰቱ የሚችሉ የተለያዩ አደጋዎችን ለመከላከል አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ