በከተማው ካነጋገርናቸው ሴቶች መካከል ወ/ሮ እጅጋየሁ ይማምና ብርቱካን አወቀ እንደተናገሩት በተለይም የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ ብሎም የራሳቸውንና የልጆቻቸውን ጤና ለመጠበቅ በልማት ሕብረት ተደራጅተው በመስራት ውጤታማ መሆን መቻላቸውን ነው የገለጹት።
ቀደም ሲል ከነበረባቸውን የጠባቂነትና የተረጅነት ስሜት በመላቀቅና በሌማት ትሩፋት ዘርፍ በትጋት ሠርተው ኢኮኖሚያቸውን ማሳደግ መቻላቸውን ጠቁመዋል።
በልማቱ ተሳታፊና ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ በትኩረት በመስራት የጓሮ አትክልቶችን ካሮት፣ ሰላጣ፣ ቀይሰር፣ አበባ ጓመንና የመሳሰሉትን በማልማት ተጠቃሚ የሆኑ ሴቶች ለቀጣይም ተለዋጭ ቦታቸውን ለማልማት ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን አስረድተዋል።
የይርጋጨፌ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፖርቲ ጽህፈት ቤት የሴቶች ሊግ ሀላፊ ወ/ሮ አማረች ኦብሴ በ2016 ዓ.ም ከ800 በላይ ሴቶች ወደ ስራ መግባታቸውንና ውጤታማ መሆናቸውን አመላክተዋል።
በተለይም ከተማ አሰተዳደሩ ለችግኝ ግዥ 250 ሺህ ብር ድጋፍ በማድረጉና ቦታ በማዘጋጀቱ ሴቶች ‹‹ምግቤን ከጓሮዬ ጤናዬን ከደጄ›› በሚል ከምግብነትም አልፎ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን አስረድተዋል።
የይርጋጨፌ ከተማ ሴቶችና ህፃናት ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ውቢት ደንቢ ሴቶቸ ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየሰሩ መሆናቸውንና በቀጣይም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አመላክተዋል።
ዘጋቢ ፡ ጽጌ ደምሴ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምርጫ ማኒፌስቶ፣ የዕጩ ማስተዋወቂያ እንዲሁም የምርጫ ቅስቀሳ ፕሮግራም በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ አካሄደ
ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጥራት ያለው የአይን ህክምና በሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ
ብልጽግና ፓርቲ የማህበረሰቡ ችግር የሚቀርፉ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ በማጠናቀቅ በውጤታማነት ለአገልግሎት እያበቃ ነው – ዶ/ር መሀመድ ኑርዬ