በኣሪ ዞን በመስጅደ ሠላምማዕድ ማጋራት መርሀግብረ ተካሄደ፡፡
በሁሉም የእምነት ተቋማት አስተምህሮ ስለ ሠላም፣ አንድነትና አብሮነት ብሎም የተቸገሩትን መርዳትና መደገፍ የፈጣሪ ትዕዛዝ በመሆኑ ማንኛውም ዜጋ ይህንን በጎ ሥራ አጠናክሮ መቀጠል ይገባል ሲሉ የመርሀግብሩ አስተባባሪ አቶ ይማም ስዒድ ተናግረዋል ።
በጂንካ ከተማ የሠላም መስጅድ ኢማም ሸህ እንዲሪስ አህመድ በጎ ሥራ ሁሌም የሚተገበር እንጂ በዓላትን ጠብቀን ብቻ የምናደርገው ሊሆን አይገባም ብለዋል፡፡
ይህ በማድረጋችን ከአላህ ወይም ከፈጣሪ በረከትን እናገኛለን ያሉት ኢማሙ የ2017 ዓ.ም 1499ኛው መውሊድ በዓል ታሳቢ ተደርጎ ስለአብሮነትና አንድነት መገለጫ የሆነው ማዕድ ማጋራት ፕሮግራም በመስጅዱ ተግባራዊ መደረጉን ገልፀዋል።
በማዕድ ማጋራት የተካፈሉ አካላትንም አመስግነዋል ።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምርጫ ማኒፌስቶ፣ የዕጩ ማስተዋወቂያ እንዲሁም የምርጫ ቅስቀሳ ፕሮግራም በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ አካሄደ
ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጥራት ያለው የአይን ህክምና በሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ
ብልጽግና ፓርቲ የማህበረሰቡ ችግር የሚቀርፉ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ በማጠናቀቅ በውጤታማነት ለአገልግሎት እያበቃ ነው – ዶ/ር መሀመድ ኑርዬ