በኣሪ ዞን በመስጅደ ሠላምማዕድ ማጋራት መርሀግብረ ተካሄደ፡፡
በሁሉም የእምነት ተቋማት አስተምህሮ ስለ ሠላም፣ አንድነትና አብሮነት ብሎም የተቸገሩትን መርዳትና መደገፍ የፈጣሪ ትዕዛዝ በመሆኑ ማንኛውም ዜጋ ይህንን በጎ ሥራ አጠናክሮ መቀጠል ይገባል ሲሉ የመርሀግብሩ አስተባባሪ አቶ ይማም ስዒድ ተናግረዋል ።
በጂንካ ከተማ የሠላም መስጅድ ኢማም ሸህ እንዲሪስ አህመድ በጎ ሥራ ሁሌም የሚተገበር እንጂ በዓላትን ጠብቀን ብቻ የምናደርገው ሊሆን አይገባም ብለዋል፡፡
ይህ በማድረጋችን ከአላህ ወይም ከፈጣሪ በረከትን እናገኛለን ያሉት ኢማሙ የ2017 ዓ.ም 1499ኛው መውሊድ በዓል ታሳቢ ተደርጎ ስለአብሮነትና አንድነት መገለጫ የሆነው ማዕድ ማጋራት ፕሮግራም በመስጅዱ ተግባራዊ መደረጉን ገልፀዋል።
በማዕድ ማጋራት የተካፈሉ አካላትንም አመስግነዋል ።
ዘጋቢ: ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተጀመረ
የተቀናጀ የመሬት አጠቃቀም ዕቅድ ያረጁ ቡናዎችን ለማደስና አዲስ ተከላን ለማስፋፋት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
የስራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን አቅም የሚያሳድግ የ12.8 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ