ሀዋሳ፡ ነሐሴ 29/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የጂንካ ዩኒቨርስቲ በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ በኦሞ ወንዝ ሙላት ለተፈናቀሉ ወገኖች ከ600 ሺህ ብር በላይ የሚገመት የተለያዩ የምግብና የአልባሳት ድጋፍ አድርጓል።
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ከተመሠረተበት ጊዜ አንስቶ የተለያዩ ችግር ፈቺ ተግባራትን እያከናወነ ቆይቷል፡፡ አሁን ላይ በኦሞ ወንዝ ሙላት ለተፈናቀሉ የዳሰነች ማህበረሰብ ዩኒቨርሲቲው ላደረገው ድጋፍ ምስጋና ያቀረቡት በዞኑ የዳሰነች ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ዑመር ነኩዌ ናቸው።
በተከሰተው ችግር ከ5ሺህ በላይ አርብቶ አደሮች መፈናቀላቸውንም ምክትል አስተዳዳሪው ገልጸዋል።
የጂንካ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አምባ ጩፋ እንደገለፁት ዩኒቨርስቲው በተለያዩ አካባቢዎች ከሚከሰቱ ድንገተኛ አደጋዎች ሕብረተሰቡን ለመታደግ ሀላፊነቱን ሲወጣ ቆይቷል።
ዩኒቨርስቲዉ በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ በኦሞ ወንዝ ሙላት ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች ከ600 ሺህ ብር በላይ የሚገመት የተለያዩ የምግብና አልባሳት ቁሳቁሶችን ድጋፍ ማድረጉን ተናግረዋል።
ሀላፊው አያይዘው በወንዙ ሙላት ምክንያት በነዋሪዎች ላይ የሚከሰተውን ተደጋጋሚ ችግሮች መቅረፍ ይቻል ዘንድ ዩኒቨርሲቲዎች በተቀናጀ አግባብ በማጥናት መፍትሔ መሻት አለባቸው ብለዋል።
ዘጋበቢ፡ ዳኜ ጥላሁን – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
2ኛ ዙር የማኅበራዊ ሳይንስ የትምህርት ዘርፍ የ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና እየተሰጠ ነው
የሚገነቡ የልማት ሥራዎች በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ ለማስቻል ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ
ከተሞችን ለነዋሪዎች ጽዱ፣ ውብና ምቹ ለማድርግ በቆሻሻ አወጋገድና አያያዝ ሥርዓት ላይ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከተማና መሠረት ልማት ቢሮ አሳሰበ