ሀዋሳ፡ 28/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) መንግሥት በህዝቦች መከከል ዘላቂ ሰላምን ለማስፈንና የህዝቦች መተማመን እንዲኖር ምክክርን ባህል ማድረግ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) ገልጸዋል:፡
የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አጀንዳ ማሰባሰብ ስራውን ከተመራጮችና ከመንግስት ባለድርሻ አከላት ጋር ቀጥለዋል።
የምክክሩ ተሳታፊዎች አካታችነት፣ ግልፀኝነትን፣ አሳታፊነትንና ተዓማኒነትን መሰረት በማድረግ ለምክክሩ ስኬት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማበርከት እንደሚጠበቅባቸውም ተገልጿል።
በምክክር መድረኩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንደሻው ጣሰው፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ ዶክተር ዲላሞ ኦቶሬ፣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ(ዶ/ር) ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች፣ የሶስቱ የመንግስት አካላት ተወካዮች፣ የሀይማኖት ተቋማት እና ማህበራት ተወካዮች እንዲሁም ታዋቂ እና ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ተወካዮች እየተሳተፉ ነው።
ዘጋቢ: በየነ ሰላሙ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ