ሀዋሳ: ነሐሴ 24/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ገቢን አሟጦ መሰብሰብ እንደሚገባ የአሪ ዞን አስተዳደር አስታወቀ።
የዞኑ ገቢዎች መምሪያ ከዞን ማዕከል፣ ወረዳዎችና የከተማ አስተዳር ባለድርሻ አካላት ጋር በገቢ ተግባራት ዙሪያ በጂንካ ከተማ ውይይት እያደረገ ይገኛል።
በመድረኩ የተገኙት የዞኑ ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሕዝቀለሰ ጋርታ ላለፉት ተከታታይ ጊዜያት የዞኑ ገቢ አፈፃፀም መሻሻል ማሣየቱን ጠቅሰው የገቢ አሰባሰቡን ማዘመን፣ የግብር ከፋዩ ግንዛቤ መሻሻልና የባለድርሻ ቅንጅታዊ አሰራር ለአፈፃፀሙ መሻሻል ምክንያት እንደነበር አመላክተዋል።
በ2017 በጀት አመት አንዳንድ በዘርፉ የሚስተዋሉ የአመለካከትና አፈፃፀም ችግሮችን በመቅረፍ በአጠቃላይ ከ876 ሚሊዮን 471ሺህ ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሠራ እንዳለ አመላክተዋል።
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብረሃም አታ ለልማትና መልካም አስተዳደር ጉዳዮች ምላሽ ለመስጠት የውስጥ ገቢ አቅምን አሟጦ መሰብሰብ ወሳኝ በመሆኑ በቀጣይ በዞኑ ያሉ የገቢ ባለድርሻ አካላት ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ ይገባል ብለዋል።
ዘጋቢ: መልካሙ ቡርዝዳቦ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ በተካሄደው ጥናት ዙሪያ በወልቂጤ ከተማ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን የጋሞ ዞን ፍትህ መምሪያ በርካታ ተግባራትን ማከናወን እንደሚጠበቅበት ተገለጸ
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ