ሀዋሳ፡ ነሐሴ 23/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ከሕዝቡ የሚነሡ የመልካም አስተዳደርና የልማት ችግሮችን በየደረጃው ምላሽ ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን በደቡብ ኦሞ ዞን የማሌ ወረዳ የሕዝብ ተወካዮች ገለጹ፡፡
ሕብረተሰቡን ቀርቦ የማናገርና አስፈፃሚውን አካል ክትትልና ቁጥጥር የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተመላክቷል፡፡
ህዝብ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች በሂደት ምላሽ እንዲያገኙ ለማድረግ የድርሻቸውን እንደሚወጡ የሕዝብ ተወካዮቹ ተናግረው፥ በኑሮ ውድነት፣ በሠላምና ፀጥታ፣ በፕሮጀክቶች መጓተት፣ በመሠረተ ልማት ግንባታና በለሎችም ችግሮች ዙሪያ ለመፍትሔ እንደሚሰሩ ገልፀዋል፡፡
የቃቆ ሳውላ ዎሞሮ ዳገት ፈጥኖ እንዲያልቅ የፌደራልና የክልል መንግሥት ትኩረትን ይሻል ያሉት የማሌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አልጋጋ ባልንሴ የኮይቤ ሴሮ ወንዝ ድልድይ በፍጥነት ወደ ሥራ እንዲገባ መወሰኑን ተናግረዋል፡፡
የመንገድ ልማቱ የእናቶችና የህፃናትን ህይወት በመታደግ፣ የወረዳ ቀበሌዎችን ከወረዳውና ከዞኑ እንዲሁም ክልል ከተማዎች ጋር የሚያገናኝ ብቸኛ መንገድ በመሆኑ ትኩረት እንዲሰጠው የወረዳዋ ነዋሪዎች ጠይቀዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
የምስራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት (ኢጋድ) አባል ሀገራት ኘሮጀክት አስተባባሪዎች እና የግብርና ሚንስቴር ብሔራዊ ኘሮጀክት ልዑክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን የድርቅ መቋቋሚያና ዘላቂ የአርብቶ አደር ኑሮ ማሻሻያ ኘሮጀክት የተሰሩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
የከተማዋን መሠረተ ልማት ለማስፋፋት በሚደረገው ሂደት የሚጠበቅባቸውን እንደሚወጡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የቀለጣ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ
ዲጂታል ኢትዮጵያን የመፍጠሪያ ጊዜን በማፋጠን ኢትዮጵያን የመጪው ዘመን መሪ ለማድረግ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ