ሀዋሳ፡ ነሐሴ 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ለ2016/17 መኸር ወቅት የእርሻ ስራቸው ማዳበርያ ባለመቅረቡ መቸገራቸውን የቡርጂ ዞን አርሶ አደሮች ተናገሩ፡፡
የዞኑ ግብርና መምሪያ በበኩሉ አርሶአደሮች የሚያነሱት ቅሬታ ተገቢ መሆኑን በማመን ችግሩን ለመቅረፍ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ጥረት እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡
አርሶ አደር ጨሜ ጨቶ እና ሾጋ አኖ የሐርዎንጄና የሬለያ ጎቼ ኩሮ ቀበሌ ነዋሪዎች ናቸው፡፡ ለመኸር ወቅት የማሳ ዝግጅት አጠናቀው መዝራት እንዳይጀምሩ የማዳበሪያ አለመቅረብ የአዝመራ ወቅቱን እንዳይጠቀሙ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል፡፡
ማሳችን ማዳበሪያ የለመደ በመሆኑ ያለ እሱ ምርት አይታሰብም ያሉት አርሶ አደሮቹ መንግሥት የዘር ወቅት ሳያልፍ በአፋጣኝ እንዲያመጣላቸውም ጠይቀዋል፡፡
አቶ ህርቦ ቤጦ የቡርጂ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ በበኩላቸው ከግብአት አቅርቦት ጋር ተያይዞ አርሶ አደሮች የሚያነሷቸው ቅሬታዎች ትክክል መሆኑን አንስተዋል፡፡ 10 ሺህ 500 ኩንታል Npsb እና 5 ሺህ 500 ዩሪያ የታቀደ ቢሆንም እስካውን የደረሰው 4 ሺህ 32 ኩንታል ዳፕና 420 ኩንታል ዩሪያ ብቻ በመሆኑ ካለው ፍላጎት ጋር መጣጣም ባለመቻሉ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
ችግሩን ለመፍታት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅርበት እየተሠራ እንደሆነ ያነሱት ኃላፊው ክልሉ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ማዳበሪያ ለማግኘት የሚያደርጉትን ጥረት አጠናክረው እንደሚቀጥሉና ለአርሶአደሮችም የዘር ወቅት በመሆኑ ያላቸውን አማራጮች ሁሉ እንዲጠቀሙ የማድረግ ሥራ እንደሚሠሩ አስታውቀዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ዮሴፍ ቶልኬ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ በተካሄደው ጥናት ዙሪያ በወልቂጤ ከተማ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን የጋሞ ዞን ፍትህ መምሪያ በርካታ ተግባራትን ማከናወን እንደሚጠበቅበት ተገለጸ
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ