ሀዋሳ፡ ነሐሴ 22/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) “የጊፋታ ዕሴቶች ለሁለንተናዊ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል የዘንድሮ የወላይታ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል እንደሚከበር የወላይታ ዞን ዋና አስተዳደር አስታውቋል::
በ2017 ዓ.ም የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓል ዘንድሮ በመስከረም 12 ላይ ይከበራል።
የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ፎላ በምክክር መድረኩ ላይ እንደገለጹት የጊፋታ በዓል ሕዝባዊና በጉጉት የሚጠበቅ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
“የጊፋታ ዕሴቶች ለሁለንተናዊ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል የዘንድሮ የወላይታ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል እንደሚከበር አስተዳዳሪው አስታውቀዋል፡፡ ከወትሮ በተለየ ሁኔታ በአሉን ለማክበር ቅንጅታዊ አሠራር እንደሚጠይቅ አስረድተዋል።
በወላይታ ብሔር ዘንድ ጊፋታ የአሮጌው ዓመት ማብቂያ እና የአዲሱ ዓመት መጀመሪያ የመሸጋገሪያ በዓል ነው፡፡
በዓሉን የማስተዋወቅ ሥራ በሚዲያ በመታጀብ ሊሠራ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ሕዝቡ የራሱን ማንነት መገለጫ መሆኑን በማመን ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል እስከ በዓሉ ዕለት ድረስ ለበዓሉ ድምቀት የድርሻውን መወጣት ይኖርበታል ብለዋል ።
የጊፋታ በዓል አከባበር ምክንያት በማድረግ የሚከናወኑ ሁነቶች ዙሪያ በቂ ቅድመ ዝግጅት መደረግ እንዳለበትም ጠቁመዋል ።
አቶ ተሾመ ሃብቴ የወላይታ ዞን ባህልና ቱርዝም መምሪያ ኃላፊ የዘንድሮው ጊፋታ በመስከረም 12/2017 ዓ.ም በድምቀት እንደሚከበር አንስተው በአሉ ባህልንና ሐይማኖትን ጋር የማይጻረር የወላይታ ሕዝብ ማንነት መገለጫ ነው ብለዋል።
ዘጋቢ፡ በቀለች ጌቾ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ