የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ እና በኢፌዲሪ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ የተመራ ልዑክ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያዊ ህዝቦች ክልል በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ የአቅመ ደካሞች ቤት ግንባታ አስጀምሯል።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በታርጫ ከተማ ለአምስት አቅመ ደካሞች ዘመናዊና ሙሉ የቤት ቁሳቁሶች የተሟሉላቸው አምስት ቤቶች እንደሚገነባ አስታውቋል።
የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ከGGGI ከተሰኘ አለም አቀፍ ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ለቤቶቹ ግንባታና ለቤት ቁሳቁስ ግዥ ከ12 ነጥብ 5 ሚልዮን ብር በላይ በጀት እንደተመደበ የኢፌዲሪ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ አብራርተዋል።
በክልሉ እየተከናወነ የሚገኝ የበጎ አገልግሎት ተግባራት በርካታ ዘጎችን ተጠቃሚ እያደረገ እንደሚገኝ የገለፁት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ፤ የተጀመሩ በጎ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በመርሃግብሩ የፌደራል፣ የክልል፣ የዞንና የታርጫ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎችና የከተማው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ እታገኝ ዘነበ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ በተካሄደው ጥናት ዙሪያ በወልቂጤ ከተማ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ እንዲሆን የጋሞ ዞን ፍትህ መምሪያ በርካታ ተግባራትን ማከናወን እንደሚጠበቅበት ተገለጸ
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ