የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ እና በኢፌዲሪ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ የተመራ ልዑክ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያዊ ህዝቦች ክልል በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ የአቅመ ደካሞች ቤት ግንባታ አስጀምሯል።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በታርጫ ከተማ ለአምስት አቅመ ደካሞች ዘመናዊና ሙሉ የቤት ቁሳቁሶች የተሟሉላቸው አምስት ቤቶች እንደሚገነባ አስታውቋል።
የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ከGGGI ከተሰኘ አለም አቀፍ ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ለቤቶቹ ግንባታና ለቤት ቁሳቁስ ግዥ ከ12 ነጥብ 5 ሚልዮን ብር በላይ በጀት እንደተመደበ የኢፌዲሪ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ አብራርተዋል።
በክልሉ እየተከናወነ የሚገኝ የበጎ አገልግሎት ተግባራት በርካታ ዘጎችን ተጠቃሚ እያደረገ እንደሚገኝ የገለፁት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ፤ የተጀመሩ በጎ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በመርሃግብሩ የፌደራል፣ የክልል፣ የዞንና የታርጫ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎችና የከተማው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ እታገኝ ዘነበ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ