ሀዋሳ፡ ነሐሴ 20/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አንደኛ ዓመት የምስረታ በዓል በወላይታ ሶዶ ከተማ በደማቅ ስነ-ስርዓት በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው፡፡
ክልሉን የሰላም የመቻቻልና የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ ላለፈው አንድ ዓመት ስራዎች ተሰርተዋል ያሉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ፈተናዎች ቢኖሩም የክልሉን ህዝቦች አብሮነትና መቻቻል አጠናክሮ ማስቀጠል ተችሏል ብለዋል።
ለዚህም የሃገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት መሪዎች ላቅ ያለ ሚና እንደነበራቸው ርዕሰ መስተዳድሩ አንስተዋል።
ክልሉን ያጋጠሙ የተፈጥሮ አደጋዎችን ተከትሎ መላው ኢትዮጵያዊያን የአደጋ ሰለባዎችን በማፅናናትና በመደገፍ ረገድ ለተደረገው ርብርብ አቶ ጥላሁን አመስግነዋል።
የክልሉን የመልካም አስተዳደርና የመሰረተ ልማት ጥያቄዎችን ለመፍታት የጋራ ርብርብ የሚጠይቅ በመሆኑ በቀጣይ የህዝብ ጥያቄን በመመለስ ላይ ትኩረት ይደረጋል ብለዋል ርዕሰ መስተዳድሩ::
ዘጋቢ፡ ሲሳይ ደበበ

More Stories
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ