ሀዋሳ፡ ነሐሴ 20/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በ2017 የትምህርት ዘመን 56 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ለመቀበል አቅዶ በምዝገባ ሂደት ላይ መሆኑን የኮሬ ዞን ትምህርት መምሪያ አስታወቀ።
የኮሬ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ታደለ አሸናፊ እንደገለጹት በ2017 የትምህርት ዘመን ቅድመ መደበኛና ጎልማሳን ጨምሮ 56 ሺህ 361 ተማሪዎችን ለመቀበል አቅዶ ምዝገባ እያካሄዱ መሆኑን ተናግረዋል።
በዞኑ 83 መደበኛ ትምህርት ቤቶች እንደሚገኙና በሁሉም አከባቢዎች ምዝገባ እየተካሄደ መሆኑን የተናገሩት አቶ ታደለ የመማር ማስተማር ተግባር በተያዘው የጊዜ ሰሌዳ ተግባራዊ እንዲሆንና የተጀመረው የተማሪዎች ምዝገባና የዝግጅት ምዕራፍ ከወዲሁ መጠናቀቅ ይገባዋል ብለዋል።
በዞኑ የዶንሶ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህርና የተማሪዎች ምዝገባ ፈፃሚ መምህር መስፍን ብርሀኑ ለምዝገባ የተፈቀደው ጊዜ ረጅም በመሆኑ በቀን ውስጥ የሚመዘገቡ ተማሪዎች ቁጥር ከወትሮው ዝቅተኛ እንደሆነ ነው የገለጹት።
በኬሌ ሙሉ 1ኛ ደረጃ እና ዶንሶ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሲመዘገቡ አግኝተን ካነጋግረናቸው ተማሪዎች ቤዛዊት እንግዳየሁ እና ግሩም አወቀ የተማሪዎች በጊዜ መመዝገብ በወላጆች የትምህርት ቁሳቁስ መሟላትና የትምህርት ቤቶች ዝግጅት ለትምህርት ሥራ ወሳኝ ነው ብለዋል፤ ዕለቱን በጉጉት እንደሚጠብቁ በመግለጽ።
ዘጋቢ: ምርጫ መላኩ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ