የተተከሉ ችግኞች ፀድቀው ለተፈለገው ዓላማ እንዲውሉ ለማስቻል መንከባከብ እንደሚገባ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ዶክተር አማረች በካሎ አሳስበዋል
የአንድ ጀንበር አረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ በዳውሮ ዞን ማረቃ ወረዳ ያካሄዱት በኢፌዲሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ኢንዱስትሪና ማዕድን ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶክተር አማረች በካሎ የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ከተጀመረ ወዲህ በአካባቢ አየር ጥበቃ ላይ ከፍተኛ ጥቅም እያገኘን ነው ብለዋል።
ዘንድሮም በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተተገበረ በሚገኘው የተከላ መርሃግብር በማረቃ ወረዳ በርካታ የማህበረሰብ ክፍሎች በመሳተፋቸው አመስግነዋል።
በተካሄደው የተከላ መርሃግብር ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉ ቢሆንም የተተከሉ ችግኞች ተጠብቀው ለተፈለገው ዓላማ እንዲውሉ ለማስቻል ደግሞ ከአካባቢው ማህበረሰብ ከፍተኛ ሀላፊነት የሚጠበቅ መሆኑን ገልጸዋል።
ከማህበረሰቡ ባለፈም የዘርፉ ተቋማትም የጥበቃና እንክብካቤ ተግባራትን በትኩረት መስራት እንደሚገባም ዶክተር አማረች አሳስበዋል።
ዘጋቢ፡ ዮሐንስ መካሻ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ