የችግኝ ተከላ ፕሮግራሙን በንግግር የከፈቱት የኮሬ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አስታረቀኝ አንደባ በሀገር ደረጃ በአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ከዞኑ በተለዩ 8 ማዕከላት የተለያዩ የችግኝ ዓይነቶች መተከላቸውን ገልጸዋል።
አክለውም የሚተከሉ ችግኞች የአየር መዛባትና የአፈር መሸርሸር ከመከላከል ባሻገር ምርትና ምርታማነትን በመሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ስላለው አንድ ቀን መትከል ብቻ ሳይሆን ቀጣይነት ያለው ተግባር መሆኑንም አስረድተዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ ዶክተር እንዳልካቸው ጌታቸው በመርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ችግኝ ተከላ እንደ ሀገር ታሪክ የምንተክልበትና ትውልድን የምናፀናበት በመሆኑ ቀጣይነት ባለው ሁኔታ አንድ ሆንን የብልጽግናን ራዕይን እናሳካለን ብለዋል።
ከአካባቢ አባቶች አቶ ኃይሌ ሉታ ጠብቀው ያቆዩት ቅርሶችና ዛሬ ላይ እየተተከሉ ያሉ ችግኞችን ወጣቱ ትውልድ በመንከባከብ በዘላቂነት አንዲያቆይ አደራ አስተላልፈዋል።
ከመርሐ ግብሩ ተሳታፊዎች መካከል ወ/ሮ ታመነች ታሪኩና ሌሎች የችግኝ ተከላ ፕሮግራም ለአከባቢው ያለውን ጠቀሜታ በመገንዘብ አሻራቸውን ማሳረፋቸውን ተናግረዋል።
ዘጋቢ: ምርጫ መላኩ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ