በማህበረሰቡ ዘንድ ችግኝ የመትከልና የማልማት ባህል እየዳበረ በመምጣቱ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ

እንደሀገር በተለያዩ ዝግጅቶች ችግኝ የመትከልና የማልማት ባህል ከጊዜ ወደጊዜ ልምድ እየሆነ በመምጣቱ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ በኣሪ ዞን በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ላይ በክብር እንግድነት የተሳተፉት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶክተር አበባየሁ ታደሰ ገልፀዋል።

ኢትዮጵያን አረንጓዴ ማልበስ ከፖለቲካ በዘለለ በዓለም ደረጃ በመልካም ተግባር ማስተዋወቅ በመሆኑ መርሀግብሩን በተገቢው ማከናወን ይገባል ብለዋል።

በኣሪ ዞን በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ላይ የተሳተፉ የሕብረተሰብ ክፍሎችም እየተተከሉ ያሉትን ዘርፈብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች አስፈላጊውን እንክብካቤ በማድረግ ለአገልግሎት እንዲበቃ የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚያበረክቱም ተናግረዋል።

ዘጋቢ፡ ዳኜ ጥላሁን – ከጂንካ ጣቢያችን