እንደሀገር በተለያዩ ዝግጅቶች ችግኝ የመትከልና የማልማት ባህል ከጊዜ ወደጊዜ ልምድ እየሆነ በመምጣቱ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ በኣሪ ዞን በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ላይ በክብር እንግድነት የተሳተፉት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶክተር አበባየሁ ታደሰ ገልፀዋል።
ኢትዮጵያን አረንጓዴ ማልበስ ከፖለቲካ በዘለለ በዓለም ደረጃ በመልካም ተግባር ማስተዋወቅ በመሆኑ መርሀግብሩን በተገቢው ማከናወን ይገባል ብለዋል።
በኣሪ ዞን በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ላይ የተሳተፉ የሕብረተሰብ ክፍሎችም እየተተከሉ ያሉትን ዘርፈብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች አስፈላጊውን እንክብካቤ በማድረግ ለአገልግሎት እንዲበቃ የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚያበረክቱም ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ ዳኜ ጥላሁን – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ