እንደሀገር በተለያዩ ዝግጅቶች ችግኝ የመትከልና የማልማት ባህል ከጊዜ ወደጊዜ ልምድ እየሆነ በመምጣቱ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ በኣሪ ዞን በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ላይ በክብር እንግድነት የተሳተፉት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶክተር አበባየሁ ታደሰ ገልፀዋል።
ኢትዮጵያን አረንጓዴ ማልበስ ከፖለቲካ በዘለለ በዓለም ደረጃ በመልካም ተግባር ማስተዋወቅ በመሆኑ መርሀግብሩን በተገቢው ማከናወን ይገባል ብለዋል።
በኣሪ ዞን በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ላይ የተሳተፉ የሕብረተሰብ ክፍሎችም እየተተከሉ ያሉትን ዘርፈብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች አስፈላጊውን እንክብካቤ በማድረግ ለአገልግሎት እንዲበቃ የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚያበረክቱም ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ ዳኜ ጥላሁን – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት በማጠናከር ክልላዊ አንድነትን ማጎልበት እንደሚገባ ተገለጸ
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ