ሀዋሳ፡ ነሃሴ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በምስራቅ ጉራጌ ዞን በቡታጅራ ከተማ በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኝ የመትከል መርሀ ግብር እየተከናወነ ነው፡፡
እንደ ሀገር በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኝ የመትከል መርሀግብር በምስራቅ ጉራጌ ዞን በቡታጅራ ከተማ በደማቅ ስነስርዓት በመከናወን ላይ ይገኛል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ታጁ ነሥሩ፣ የቡታጅራ ከተማ ከንቲባ አቶ አብዶ አህመድ፣ የከተማው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሳሙኤል ማርቆስን ጨምሮ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ የዞንና የከተማው አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ነዋሪዎችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።
የችግኝ ተከላ መርሀ ግብሩ እስከ ምሸቱ 12 ሰአት እንደሚቀጥል ተገልጿል።
ዘጋቢ፡ ትግስት ተሾመ – ከወልቂጤ ጣቢያችን
More Stories
አካል ጉዳተኞች መብቶቻቸውና ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ በቅንጅትና በጥምረት መስራት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለፀ
አካባቢን በመጠበቅና በማጽዳት ምቹና ጽዱ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ሁሉም የድርሻውን ልወጣ እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ
ግለሰባዊ ነጠላ ትርክቶችን በጋራ በመታገል በመደመር እሳቤ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ ተገለጸ