ሀዋሳ፡ ነሃሴ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በምስራቅ ጉራጌ ዞን በቡታጅራ ከተማ በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኝ የመትከል መርሀ ግብር እየተከናወነ ነው፡፡
እንደ ሀገር በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኝ የመትከል መርሀግብር በምስራቅ ጉራጌ ዞን በቡታጅራ ከተማ በደማቅ ስነስርዓት በመከናወን ላይ ይገኛል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ታጁ ነሥሩ፣ የቡታጅራ ከተማ ከንቲባ አቶ አብዶ አህመድ፣ የከተማው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሳሙኤል ማርቆስን ጨምሮ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ የዞንና የከተማው አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ነዋሪዎችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።
የችግኝ ተከላ መርሀ ግብሩ እስከ ምሸቱ 12 ሰአት እንደሚቀጥል ተገልጿል።
ዘጋቢ፡ ትግስት ተሾመ – ከወልቂጤ ጣቢያችን
More Stories
የምስራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት (ኢጋድ) አባል ሀገራት ኘሮጀክት አስተባባሪዎች እና የግብርና ሚንስቴር ብሔራዊ ኘሮጀክት ልዑክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን የድርቅ መቋቋሚያና ዘላቂ የአርብቶ አደር ኑሮ ማሻሻያ ኘሮጀክት የተሰሩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
የከተማዋን መሠረተ ልማት ለማስፋፋት በሚደረገው ሂደት የሚጠበቅባቸውን እንደሚወጡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የቀለጣ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ
ዲጂታል ኢትዮጵያን የመፍጠሪያ ጊዜን በማፋጠን ኢትዮጵያን የመጪው ዘመን መሪ ለማድረግ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ