ሀዋሳ፡ ነሃሴ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በምስራቅ ጉራጌ ዞን በቡታጅራ ከተማ በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኝ የመትከል መርሀ ግብር እየተከናወነ ነው፡፡
እንደ ሀገር በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኝ የመትከል መርሀግብር በምስራቅ ጉራጌ ዞን በቡታጅራ ከተማ በደማቅ ስነስርዓት በመከናወን ላይ ይገኛል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ታጁ ነሥሩ፣ የቡታጅራ ከተማ ከንቲባ አቶ አብዶ አህመድ፣ የከተማው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሳሙኤል ማርቆስን ጨምሮ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ የዞንና የከተማው አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ነዋሪዎችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።
የችግኝ ተከላ መርሀ ግብሩ እስከ ምሸቱ 12 ሰአት እንደሚቀጥል ተገልጿል።
ዘጋቢ፡ ትግስት ተሾመ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ