ሀዋሳ፡ ነሃሴ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በምስራቅ ጉራጌ ዞን በቡታጅራ ከተማ በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኝ የመትከል መርሀ ግብር እየተከናወነ ነው፡፡
እንደ ሀገር በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኝ የመትከል መርሀግብር በምስራቅ ጉራጌ ዞን በቡታጅራ ከተማ በደማቅ ስነስርዓት በመከናወን ላይ ይገኛል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ታጁ ነሥሩ፣ የቡታጅራ ከተማ ከንቲባ አቶ አብዶ አህመድ፣ የከተማው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ሳሙኤል ማርቆስን ጨምሮ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ የዞንና የከተማው አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ነዋሪዎችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።
የችግኝ ተከላ መርሀ ግብሩ እስከ ምሸቱ 12 ሰአት እንደሚቀጥል ተገልጿል።
ዘጋቢ፡ ትግስት ተሾመ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ