ሀዋሳ፡ ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) “የምትተክል ሀገር የሚያፀና ትውልድ” በሚል መሪ ቃል በደቡብ ኦሞ ዞን ኛንጋቶም ወረዳ በ6 ጣቢያዎች የአንድ ጀምበር አረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር እየተካሄደ ይገኛል፡፡
የችግኝ ተከላው በወረዳው በሲሳይ እርሻ ሳይት ጣቢያ 1 እና 2፣ በናሮጎይ፣ በGIZ-ጣቢያ፣ በጤና ጣቢያ እንዲሁም በካንጋቲን ሆስታል እየተተከለ ይገኛል፡፡
በመርሃ-ግብሩ የዞኑ አመራሮች፤ የወረዳው አመራርን ጨምሮ መላው የወረዳው ማህበረሰብ እየተሳተፈ ይገኛል፡፡
ዘጋቢ፡ መልካሙ ቡርዝዳቦ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ