ሀዋሳ፡ ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) “የምትተክል ሀገር የሚያፀና ትውልድ” በሚል መሪ ቃል በደቡብ ኦሞ ዞን ኛንጋቶም ወረዳ በ6 ጣቢያዎች የአንድ ጀምበር አረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር እየተካሄደ ይገኛል፡፡
የችግኝ ተከላው በወረዳው በሲሳይ እርሻ ሳይት ጣቢያ 1 እና 2፣ በናሮጎይ፣ በGIZ-ጣቢያ፣ በጤና ጣቢያ እንዲሁም በካንጋቲን ሆስታል እየተተከለ ይገኛል፡፡
በመርሃ-ግብሩ የዞኑ አመራሮች፤ የወረዳው አመራርን ጨምሮ መላው የወረዳው ማህበረሰብ እየተሳተፈ ይገኛል፡፡
ዘጋቢ፡ መልካሙ ቡርዝዳቦ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የሀዲያ ብሄር ዘመን መለወጫ “ያሆዴ“ በአልን በዩኒስኮ ለማስመዝገብ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተሰራ እንደሆነ ተገለጸ
ከ 2 ሺህ በላይ ወጣቶች የተሳተፉበት የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በስኬት ተጠናቋል – የበና ጸማይ ወረዳ አስተዳደር
የጌዴኦ ዞን ምክር ቤት 32ኛ የምክር ቤቶች የጋራ ምክክር ፎረም አካሄደ