ሀዋሳ፡ ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) “የምትተክል ሀገር፡ የሚያፀና ትውልድ” በሚል መሪ ቃል የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በደቡብ ኦሞ ዞን ማሌ ወረዳ እየተካሄደ ነው፡፡
በመላው ኢትዮጵያ በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል በወጣው እቅድ መሰረት በማሌ ወረዳ ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያላቸው ችግኞችን የመትከል መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው።
መርሐ ግብሩን የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አልጋጋ ባልንሴ ከዞኑ በመጡ ደጋፊ አመራሮች ጋር በመሆን በአሸከር ቀበሌ በመገኘት እያካሄዱ ነው።
በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በወረዳው በተለዪ 20 ቦታዎች ተከላው እየተካሄደ ይገኛል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ