ሀዋሳ፡ ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) “የምትተክል ሀገር፡ የሚያፀና ትውልድ” በሚል መሪ ቃል የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በደቡብ ኦሞ ዞን ማሌ ወረዳ እየተካሄደ ነው፡፡
በመላው ኢትዮጵያ በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል በወጣው እቅድ መሰረት በማሌ ወረዳ ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያላቸው ችግኞችን የመትከል መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው።
መርሐ ግብሩን የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አልጋጋ ባልንሴ ከዞኑ በመጡ ደጋፊ አመራሮች ጋር በመሆን በአሸከር ቀበሌ በመገኘት እያካሄዱ ነው።
በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በወረዳው በተለዪ 20 ቦታዎች ተከላው እየተካሄደ ይገኛል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
አካል ጉዳተኞች መብቶቻቸውና ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ በቅንጅትና በጥምረት መስራት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለፀ
አካባቢን በመጠበቅና በማጽዳት ምቹና ጽዱ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ሁሉም የድርሻውን ልወጣ እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ
ግለሰባዊ ነጠላ ትርክቶችን በጋራ በመታገል በመደመር እሳቤ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ ተገለጸ