ሀዋሳ፡ ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) “የምትተክል ሀገር፡ የሚያፀና ትውልድ” በሚል መሪ ቃል የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በደቡብ ኦሞ ዞን ማሌ ወረዳ እየተካሄደ ነው፡፡
በመላው ኢትዮጵያ በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል በወጣው እቅድ መሰረት በማሌ ወረዳ ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያላቸው ችግኞችን የመትከል መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው።
መርሐ ግብሩን የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አልጋጋ ባልንሴ ከዞኑ በመጡ ደጋፊ አመራሮች ጋር በመሆን በአሸከር ቀበሌ በመገኘት እያካሄዱ ነው።
በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በወረዳው በተለዪ 20 ቦታዎች ተከላው እየተካሄደ ይገኛል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ብልጽግና ፓርቲ የማህበረሰቡ ችግር የሚቀርፉ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ በማጠናቀቅ በውጤታማነት ለአገልግሎት እያበቃ ነው – ዶ/ር መሀመድ ኑርዬ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞን ምዕራብ አዘርነት በርበሬ ወረዳ የተለያዩ ፕሮጀክቶች የምረቃ ፕሮግራም እየተካሄደ ነው
የ3ኛው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ውድድር አማሮ ኬሌ ክለብ ሻምፒዮን ሆነ