ሀዋሳ፡ ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) “የምትተክል ሀገር፡ የሚያፀና ትውልድ” በሚል መሪ ቃል የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በደቡብ ኦሞ ዞን ማሌ ወረዳ እየተካሄደ ነው፡፡
በመላው ኢትዮጵያ በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል በወጣው እቅድ መሰረት በማሌ ወረዳ ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያላቸው ችግኞችን የመትከል መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው።
መርሐ ግብሩን የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አልጋጋ ባልንሴ ከዞኑ በመጡ ደጋፊ አመራሮች ጋር በመሆን በአሸከር ቀበሌ በመገኘት እያካሄዱ ነው።
በአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በወረዳው በተለዪ 20 ቦታዎች ተከላው እየተካሄደ ይገኛል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በግንቦት እና ሰኔ 2018 ዓ.ም ወራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ፣ በቱሪዝም፣ በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በዲጂታል ኢትዮጵያ፣ በሀገር በቀል ሪፎርም እና ቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ዙሪያ ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ክንውኖችን አድርገዋል።
በህገወጥ መንገድ ከሀገር መውጣት ከህግ፣ ከደህንነት እና ከማህበራዊ አንፃር ከባድ ችግሮችን እንደሚያስከትል ተገለጸ
ወጣቶች ያላቸውን ጊዜ፣ እውቀትና ጉልበት በመጠቀም አቅመ ደካሞችንና የተቸገሩ ወገኖችን መደገፍ እንዳለባቸው ተገለፀ