ሀዋሳ፡ ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በዳውሮ ዞን በ181 ቀበሌያት የአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር እየተካሄደ ይገኛል።
በአንድ ጀንበር በዞኑ ሊተከል የታቀደው በ99 መትከያ ቦታዎች የመረጃ ቋት መዘጋጀቱን የዳውሮ ዞና ግብርና አካባቢ ጥበቃና ህብረት ሥራ መምሪያ ኃላፊ አቶ በተላ በየነ ገልፀዋል።
ለተከላ በተመረጡ ቦታዎች የችግኝ ፅድቀት መጠንን ለማሳደግ የተለያዩ አደረጃጀቶችን በማዋቀር እንዲጠበቁ ለማስቻል ታቅዶ እየተሠራበት ነው ብለዋል።
በተከላው አባቶች፣ ሴቶች ወጣቶችን ጨምሮ የተለያዩ ማህበራ መሰረቶች ተሣታፊ ሆነዋል።
አሁን ላይ በዞኑ ሊተከሉ በታቀደባቸው 181 ቀበሌያትም የችግኝ ተከላ እየተካሄደ እንደሚገኝ አቶ በተላ ገልፀዋል።
በማረቃ ወረዳ ካነጋገርናቸው በተከላው ከተሣተፉት መካከል ወ/ሮ ጌታቸው ላንጋና እና አየለች ኡማ ችግኝ መትከል ለአካባቢያችን አየር ፀባይ በጣም አስፈላጊ መሆኑን ተገንዝበን በየዓመቱ እየተከልን ቆይተናል ብለዋል።
ሀገራዊ ጥሪን ተቀብለው በአንድ ጀንበር በየግላቸው ከ15 በላይ ችግኞችን በመትከላቸው ደስተኞች መሆናቸውንም ገልፀዋል።
ዘጋቢ፡ ዮሐንስ መካሻ – ከዋካ ጣቢያችን
More Stories
የምክር ቤቶችን አቅም በማጎልበት የህዝብ ተጠቃሚነትን ማጎልበት ይገባል ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ ተናገሩ
ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ አላማ በማዋልና ገዢ ትርክትን በማስረጽ የቱሪስት መዳረሻዎችን ማስተዋወቅ እንደሚገባ ተገለጸ
በምግብ ሰብል ራስን የመቻል አቅም ማሳደግ ላይ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ