ሀዋሳ፡ ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በዳውሮ ዞን በ181 ቀበሌያት የአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር እየተካሄደ ይገኛል።
በአንድ ጀንበር በዞኑ ሊተከል የታቀደው በ99 መትከያ ቦታዎች የመረጃ ቋት መዘጋጀቱን የዳውሮ ዞና ግብርና አካባቢ ጥበቃና ህብረት ሥራ መምሪያ ኃላፊ አቶ በተላ በየነ ገልፀዋል።
ለተከላ በተመረጡ ቦታዎች የችግኝ ፅድቀት መጠንን ለማሳደግ የተለያዩ አደረጃጀቶችን በማዋቀር እንዲጠበቁ ለማስቻል ታቅዶ እየተሠራበት ነው ብለዋል።
በተከላው አባቶች፣ ሴቶች ወጣቶችን ጨምሮ የተለያዩ ማህበራ መሰረቶች ተሣታፊ ሆነዋል።
አሁን ላይ በዞኑ ሊተከሉ በታቀደባቸው 181 ቀበሌያትም የችግኝ ተከላ እየተካሄደ እንደሚገኝ አቶ በተላ ገልፀዋል።
በማረቃ ወረዳ ካነጋገርናቸው በተከላው ከተሣተፉት መካከል ወ/ሮ ጌታቸው ላንጋና እና አየለች ኡማ ችግኝ መትከል ለአካባቢያችን አየር ፀባይ በጣም አስፈላጊ መሆኑን ተገንዝበን በየዓመቱ እየተከልን ቆይተናል ብለዋል።
ሀገራዊ ጥሪን ተቀብለው በአንድ ጀንበር በየግላቸው ከ15 በላይ ችግኞችን በመትከላቸው ደስተኞች መሆናቸውንም ገልፀዋል።
ዘጋቢ፡ ዮሐንስ መካሻ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የምሁራን አንድነትን ማጠናከርና የእርስ በእርስ መከባበር ባህልን ማጎልበት ለአካባቢው ዘላቂ ሠላም መስፈን ወሳኝነት እንዳለው ተመላከተ
በብልጽግና ፓርቲ የሥራ አስተባባሪዎችና ዕጩ ወኪሎች ኃላፊነትና ግዴታ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ
የመምህራንን ኑሮ ለማሻሻል እና ሙያዊ ክብራቸውን ለመመለስ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን በቤንች ሸኮ ዞን የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር ሰለሞን ለዊ ተናገሩ