ሀዋሳ፡ ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በዳውሮ ዞን በ181 ቀበሌያት የአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር እየተካሄደ ይገኛል።
በአንድ ጀንበር በዞኑ ሊተከል የታቀደው በ99 መትከያ ቦታዎች የመረጃ ቋት መዘጋጀቱን የዳውሮ ዞና ግብርና አካባቢ ጥበቃና ህብረት ሥራ መምሪያ ኃላፊ አቶ በተላ በየነ ገልፀዋል።
ለተከላ በተመረጡ ቦታዎች የችግኝ ፅድቀት መጠንን ለማሳደግ የተለያዩ አደረጃጀቶችን በማዋቀር እንዲጠበቁ ለማስቻል ታቅዶ እየተሠራበት ነው ብለዋል።
በተከላው አባቶች፣ ሴቶች ወጣቶችን ጨምሮ የተለያዩ ማህበራ መሰረቶች ተሣታፊ ሆነዋል።
አሁን ላይ በዞኑ ሊተከሉ በታቀደባቸው 181 ቀበሌያትም የችግኝ ተከላ እየተካሄደ እንደሚገኝ አቶ በተላ ገልፀዋል።
በማረቃ ወረዳ ካነጋገርናቸው በተከላው ከተሣተፉት መካከል ወ/ሮ ጌታቸው ላንጋና እና አየለች ኡማ ችግኝ መትከል ለአካባቢያችን አየር ፀባይ በጣም አስፈላጊ መሆኑን ተገንዝበን በየዓመቱ እየተከልን ቆይተናል ብለዋል።
ሀገራዊ ጥሪን ተቀብለው በአንድ ጀንበር በየግላቸው ከ15 በላይ ችግኞችን በመትከላቸው ደስተኞች መሆናቸውንም ገልፀዋል።
ዘጋቢ፡ ዮሐንስ መካሻ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ መንግሥት ወቅቱን የጠበቀና ጥራት ያለው ውሳኔ እንዲሰጥ የሚያስችል መሆኑን በኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት የአርባምንጭ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ገለፀ
የጎርፍ መውረጃ ቦይ አለመሠራት በቤት ንብረታቸው ላይ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን በከምባታ ዞን የዳምቦያ ከተማ አስተዳደር የ02 ቀበሌ ነዋሪዎች ገለጹ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የፕላን መሰረተ ልማት እና የመንግስት ሀብት አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በአርባ ምንጭ ከተማ የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ግማሽ አመት የተከናወኑ ተግባራትን የመስክ ምልከታ አደረገ