ሀዋሳ፡ ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በዳውሮ ዞን በ181 ቀበሌያት የአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር እየተካሄደ ይገኛል።
በአንድ ጀንበር በዞኑ ሊተከል የታቀደው በ99 መትከያ ቦታዎች የመረጃ ቋት መዘጋጀቱን የዳውሮ ዞና ግብርና አካባቢ ጥበቃና ህብረት ሥራ መምሪያ ኃላፊ አቶ በተላ በየነ ገልፀዋል።
ለተከላ በተመረጡ ቦታዎች የችግኝ ፅድቀት መጠንን ለማሳደግ የተለያዩ አደረጃጀቶችን በማዋቀር እንዲጠበቁ ለማስቻል ታቅዶ እየተሠራበት ነው ብለዋል።
በተከላው አባቶች፣ ሴቶች ወጣቶችን ጨምሮ የተለያዩ ማህበራ መሰረቶች ተሣታፊ ሆነዋል።
አሁን ላይ በዞኑ ሊተከሉ በታቀደባቸው 181 ቀበሌያትም የችግኝ ተከላ እየተካሄደ እንደሚገኝ አቶ በተላ ገልፀዋል።
በማረቃ ወረዳ ካነጋገርናቸው በተከላው ከተሣተፉት መካከል ወ/ሮ ጌታቸው ላንጋና እና አየለች ኡማ ችግኝ መትከል ለአካባቢያችን አየር ፀባይ በጣም አስፈላጊ መሆኑን ተገንዝበን በየዓመቱ እየተከልን ቆይተናል ብለዋል።
ሀገራዊ ጥሪን ተቀብለው በአንድ ጀንበር በየግላቸው ከ15 በላይ ችግኞችን በመትከላቸው ደስተኞች መሆናቸውንም ገልፀዋል።
ዘጋቢ፡ ዮሐንስ መካሻ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የከተማውን መሰረተ ልማት ከማሟላት ባሻገር ለነዋሪዎች ምቹ እና ማራኪ በማድረግ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
የዱራሜ ከተማ የኮሪደር ልማት ሥራ በአዲስ መልክ በዘመናዊ ዲዛይን እየተሰራ መሆኑን የዱራሜ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በጎ ተግባር ወቅትን ጠብቆ የሚተገበር ብቻ ሳይሆን የሁልጊዜ ተግባራችንና ባህላችን ልናደርገው ይገባል -ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ