ሀዋሳ፡ ነሐሴ16/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በነገው እለት በአንድ ጀንበር ለሚተከለው የችግኝ ተከላ ዘመቻ አስፈላገውን ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን በምእራብ ኦሞ ዞን የማጂ እና የመኢኒት ሻሻ ወረዳዎች ገለጹ።
የአረንጓዴው አሻራ መረሀግብር አንዱ አካል የሆነው እና እንደ ሀገር 600 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል የተያዘውን እቅድ ለማሳካት በሁሉም አከባቢዎች ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የገለጹት የወረዳው ግብርናና አከባቢ ጥበቃ ህብረት ስራ ጽህፈት ቤት ሀላፊው አቶ አበበ ባቡ የተናገሩት።
እንደ እርሳቸው ገለጻ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው የተለያዩ የደን እና የፍራፍሬ ችግኞች ለተከላ መዘጋጀታቸውን ጠቁመው፥ ለተከላውም እስካሁን 429 ሺ ጉድጓዶች በተለዩ 14 የተከላ ቦታዎች መዘጋጀታቸውን ጠቁመዋል።
በዚህም ከ2 ሺ በላይ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚሳተፉም ተናግረዋል።
በተመሳሳይ በዞኑ በመኢኒት ሻሻ ወረዳ የተለያዩ የደን እና ፍራፍሬ ችግኞችን ለመትከል አስፈላጊውን ዝግጅት ማጠናቀቁን የወረዳው ግብርና አከባቢ ጥበቃ ህብረት ስራ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አየለ ዱርኩባ ተናግረዋል።
ችግኙም በተለዩ 15 ቦታዎች በ160 ሄክታር ላይ እንደሚተከል ገልጸው በተከላው በወረዳው የሚገኙ ከ20 ሺ የሚበልጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳታፊ እንደሚሆኑ ተናግረዋል።
ዘጋቢ: አብዮት በቀለ – ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
በግንቦት እና ሰኔ 2018 ዓ.ም ወራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ፣ በቱሪዝም፣ በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በዲጂታል ኢትዮጵያ፣ በሀገር በቀል ሪፎርም እና ቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ዙሪያ ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ክንውኖችን አድርገዋል።
በህገወጥ መንገድ ከሀገር መውጣት ከህግ፣ ከደህንነት እና ከማህበራዊ አንፃር ከባድ ችግሮችን እንደሚያስከትል ተገለጸ
ወጣቶች ያላቸውን ጊዜ፣ እውቀትና ጉልበት በመጠቀም አቅመ ደካሞችንና የተቸገሩ ወገኖችን መደገፍ እንዳለባቸው ተገለፀ