የቤንች ሸኮ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 11ኛ አመት ስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤውን በሚዛን አማን ከተማ በማካሄድ ላይ ይገኛል።
የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ጌድዮን ኮስታብ እንደተናገሩት፤ ምክር ቤቶች የዞኑ ህዝብ የሉዓላዊነት መገለጫ ናቸው።
በየደረጃዉ የሚገኙት ምክር ቤቶች በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ እና በመንግሥት አሰራር ዉስጥ የሕዝቡን ተሳትፎና ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ተግባራትን በማከናወን ህገ-መንግስታዊ ግዴታቸውን ሊወጡ ይገባል ሲሉም ነዉ ዋና አፈ ጉባኤዉ የጠቆሙት።
ምክር ቤቱ የሚወጡ ህጎችን በዞኑ በየደረጃው የሚገኙ ምክር ቤቶች በተገቢው እንዲተገበሩ አስፈፃሚ አካላትን በመከታተል በቀጣይ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል።
ምክር ቤቱ በጉባኤው የዞኑን የአስተዳደር ምክር የ2016 ዓ.ም ዕቅድ አፈጻጸምና የ2017 ዓ.ም መሪ ዕቅድ ላይ ተወያይቶ ያፀድቃል።
በመጨረሻም በዞኑ በቅርቡ የተዋቀሩትን የሸኮ እና የቢፍቱ ከተማ አስተዳደሮች የመዋቅር ጉዳይ በጉባኤ ቀርቦ የሚፀድቅ ሲሆን የተለያዩ ሹመቶች እንደሚኖሩም የጉባኤው መርሃ-ግብር ያሳያል።
ዘጋቢ፡ ጦያር ይማም – ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
በቡና ዘርፍ ያለውን ህገወጥ ንግድ በጋራ መግታት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የቡና ማህበር ገለጸ
6ኛው ሀገር አቀፍ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ የሰላም ኮንፍረንስ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ በተለያዩ ዝግጅቶች በአብዮ ኤርሳሞ መታሰቢያ ስታዲየም እየተካሄደ ነው
የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች መንግስት በከተማና በገጠር ለጀመራቸው የልማት እንቅስቃሴዎች ዋነኛ ሞተሮች ናቸው – አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር)