የቤንች ሸኮ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 11ኛ አመት ስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤውን በሚዛን አማን ከተማ በማካሄድ ላይ ይገኛል።
የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ጌድዮን ኮስታብ እንደተናገሩት፤ ምክር ቤቶች የዞኑ ህዝብ የሉዓላዊነት መገለጫ ናቸው።
በየደረጃዉ የሚገኙት ምክር ቤቶች በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ እና በመንግሥት አሰራር ዉስጥ የሕዝቡን ተሳትፎና ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ተግባራትን በማከናወን ህገ-መንግስታዊ ግዴታቸውን ሊወጡ ይገባል ሲሉም ነዉ ዋና አፈ ጉባኤዉ የጠቆሙት።
ምክር ቤቱ የሚወጡ ህጎችን በዞኑ በየደረጃው የሚገኙ ምክር ቤቶች በተገቢው እንዲተገበሩ አስፈፃሚ አካላትን በመከታተል በቀጣይ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል።
ምክር ቤቱ በጉባኤው የዞኑን የአስተዳደር ምክር የ2016 ዓ.ም ዕቅድ አፈጻጸምና የ2017 ዓ.ም መሪ ዕቅድ ላይ ተወያይቶ ያፀድቃል።
በመጨረሻም በዞኑ በቅርቡ የተዋቀሩትን የሸኮ እና የቢፍቱ ከተማ አስተዳደሮች የመዋቅር ጉዳይ በጉባኤ ቀርቦ የሚፀድቅ ሲሆን የተለያዩ ሹመቶች እንደሚኖሩም የጉባኤው መርሃ-ግብር ያሳያል።
ዘጋቢ፡ ጦያር ይማም – ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
የአርሶ አደሩን የመሬት ሀብት ከፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ ጋር በማስተሳሰር አርሶአደሩ የፋይናንስ ተጠቃሚ እንዲሆን እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ የእናቶች ጤናና የሥርዓተ-ምግብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት የ2018 ባጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም መድረክ በሆሳዕና ከተማ እያካሄደ ይገኛል
የከተማ አስተዳደሩ ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ጽህፈት ቤት ወጣቶችን በማህበር በማደራጀት የኢኮኖሚ አቅማቸውን እንዲያጎለብቱ እያደረገ መሆኑን አስታወቀ