በክልል ደረጃ ከሚተከሉ ችግኞች 9 ነጥብ 4 ሚሊዮን የሚሆነው በሴቶች የሚሸፈን መሆኑን የሴቶች ሊግ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ሰብለጸጋ አየለ ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ከ2 ሺ 11 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ሲደረግ የቆየው የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር በሀገሪቱ የነበረውን የደን ሽፋን ከማሳደጉም በላይ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ ተጨባጭ ዉጤት ማምጣቱንም ተናግረዋል።
በመርሃ-ግብሩም ሴቶች ከፍተኛውን ድርሻ እየተወጡ መሆናቸውን የገለጹት ኃላፊዋ ለዘመቻው መሳካት በየደረጃው የሚገኙ አካላት የበኩላቸዉን አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን አስታውሰዋል።
የ2016 የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር አካል ለሆነው የ600 ሚልዮን የአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ እንደ ሀገር አስፈላጊዉ ቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ተጠናቀዋል።
ከዚህም የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል 18 ነጥብ 9 ሚሊየን ጥምር የደን ችግኞችን ለመትከል መዘጋጀቱን ከክልሉ ግብርና ቢሮ ያገኘነዉ መረጃ ያመለክታል።
በመሆኑም ሀምሌ 17 ቀን 2016 ዓመተ ምህረት በሚከናወነው የአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ የክልሉ ሴቶች በንቃት እንዲሳተፉ ለማድረግ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መደረጉንም ወ/ሮ ሰብለጸጋ ገልጸዋል።
በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች ለተከላ በተለዩ 813 ቦታዎች ከሚተከለው 18 ነጥብ 9 ችግኞች መካከል 9 ነጥብ 4 ያህሉ በሴቶች የሚከናወን ይሆናል ብለዋል።
ዘጋቢ፡ አሳምነዉ አትርሳዉ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ