ሀዋሳ፡ ነሐሴ 06/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሀዲያ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 12ኛ ዓመት 23ኛ የስራ ዘመን መደበኛ ጉበኤውን እያካሄደ ይገኛል፡፡
ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ እቴነሽ ሙሉጌታ ምክር ቤቱ ከመደበኛ ስራ ጎን ለጎን በቋሚ ኮሚቴ አማካይነት የአስፈጻሚ ተቋማትን የስራ አፈጻጸም በዓመት አራት ጊዜ ክትትልና ድጋፍ ማድረጉን አንስተዋል።
ቋሚ ኮሚቴዎቹ ባደረጉት ድጋፍና ክትትል የሕብረተሰቡ የመልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች መመለሳቸውን የተናገሩት ዋና አፈ ጉባኤዋ የኦዲት ግኝቶችን መሠረት በማድረግ ተጠያቂነት እንዲሰፍን ምክር ቤቱ የድርሻውን እንደተወጣም አንስተዋል።
ምክር ቤቱ በተያዘው በጀት ዓመት ተግባሩን የበለጠ አጠናክሮ እንደሚያስቀጥል የተናገሩት ወ/ሮ እቴነሽ የምክር ቤቱ አባላትም ሆኑ ህብረተሰቡ ሚናውን እንዲጫወት ጠይቀዋል።
በዞኑ ዋና አስተዳደሪ በአቶ ማቴዎስ አኒዮ አቅረቢነት ወ/ሮ አለምነሽ ክፍሌ በምክር ቤቱ ለምክትል አፈ ጉባኤነት የቀረቡ ሲሆን ምክር ቤቱ ሹመቱን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
ምክር ቤቱ በዛሬ ውሎው በዞኑ የ2016 በጀት ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት ዙሪያ በስፋት ተወያይቷል፡፡ በነገው ዕለት የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ2016 አፈጻጸም ሪፖርትና በ2017 ዕቅድ ዙሪያ ይመክራል፡፡
በተጨማሪም በ2017 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ላይ ተወያይት የሚያጸድቅ ሲሆን የተለያዩ ሹመቶችንም እንደሚጸድቅ ይጠበቃል።
ዘጋቢ፡ ጌታቸው መጮሮ -ከሆሳዕና ጣቢያችን
More Stories
ሀገሪቱን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በማሸጋገር በማህበራዊም ሆነ ኢኮኖሚያዊ ዘርፍ ተጠቃሚ ለማደረግ ሁሉም አካላት የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ እንደሚገባ ተጠቆመ
የክልሉን ልማትና ብልፅግና ለማረጋገጥ በ2018 በጀት አመት በተለያዩ የልማት ዘርፎች የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ምርጫ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባኤውን ከሐምሌ 10/2017 ጀምሮ እንደሚያካሂድ ተገለፀ