በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጠምባሮ ልዩ ወረዳ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ጽህፈት ቤትም በወማ በርገኖ በላንጎ ሞት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጿል።
ወማ በርገኖ በላንጎ ከአባታቸው ከአቶ በላንጎ ባዕሦ እና ከእናታቸው ወ/ሮ እንታሜ ቂዶሬ በቀድሞ ከምባታና ሀዲያ አውራጃ ኦሞ ሸለቆ ወረዳ በአሁኑ ጠምባሮ ልዩ ወረዳ ጋዕቻ ቀበሌ ሰኔ 24 ቀን 1942 ዓ.ም ተወለዱ።
ወማ በርገኖ በላንጎ ከነሐሴ 01 ቀን 1992 ዓ.ም ጀምሮ የጠምባሮን ባህላዊ አስተዳደር ንግስና (ላሂ ወማ) ማዕረግ ከተረከቡ ወዲህ ቀድሞ የነበራቸውን የህዝብ ኃላፊነት ስሜት ይበልጥ በማሳደግ በማናቸውም ህዝባዊ መድረኮች እርቅንና ፍቅርን፣ አንድነትና መቻቻልን የሚሰብኩ እንዲሁም ከመንግስት አካላት ጎን በመሆን ለአካባቢው ልማት የሚቆረቆሩ አስተዋይ አባት ነበሩ።
በባለፉት ዓመታትም ከቀድሞው የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል መንግስት ተመርጠው የክልሉን ህዝብ በመወከል በሀገራዊ የሀገር ሽማግሌዎች የጋራ ፎረም አባል በመሆን ለሀገር ዘላቂ ሠላም የድርሻቸውን የተወጡ ነበሩ።
ወማ በርገኖ በላንጎ ባለትዳርና የ2 ወንድና የ5 ሴት ልጆች አባት ሲሆኑ ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ነሐሴ 05 ቀን 2016 ዓ.ም በተወለዱ በ74 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጠምባሮ ልዩ ወረዳ የባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ወልዴ፤ ወማ በርገኖ በላንጎ ለጠምባሮ ብሔረሰብ ባህልና ታሪክ እድገት ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ አባት ከመሆንም በላይ የብሔረሰቦችን አንድነት የሚያስተሳስሩ ፍቅርና መቻቻልን የሚሰብኩ ታላቅ አባት እንደነበሩ አውስተዋል።
የጽህፈት ቤት ኃላፊው በወማ በርገኖ በለንጎ ህልፈት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልፀው ለመላው የጠምባሮ ህዝብ፣ ለቤተሰቦቻቸውና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ተመኝተዋል።
ዘጋቢ: አማኑኤል አጤቦ – ከሆሳዕና ጣቢያችን
More Stories
በካፋ ዞን ጨና ወረዳ በምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም (FSRP) የተከናወኑ የልማት ስራዎች ላይ ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ጋር የልምድ ልውውጥ ተደረገ
ሳታ ቴክኖሎጂ እና ቢዝነስ ኮሌጅ በአርባ ምንጭ ካምፓስ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች በመጀመሪያ ዲግሪ እና ቴክኒክና ሙያ ስልጠና መስኮች ያሰለጠናቸውን 2 ሺህ 132 ተማሪዎችን አስመረቀ
በዕቅድ የሚመራ የመፈፀም አቅሙ ያደገ ሲቪል ሰርቫንት ለመገንባት እየተሰራ መሆኑን በደቡብ ኦሞ ዞን የሳላማጎ ወረዳ ሲቪል ሰርቪስ ጽ/ቤት ገለፀ