የኢፌዲሪ ቱሪዝም ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በመሬት ናዳ ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የ3ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረጉ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 26/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢፌዲሪ ቱሪዝም ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በመሬት ናዳ ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የ3ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርገዋል።
የኢፌዲሪ ቱሪዝም ሚንስቴር ሚንስትር አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ በአደጋው ሳቢያ ለተጎዱ ወገኖች የተሰማቸውን ልባዊ ሐዘንም በዚህ ወቅት ገልጸዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ር/መስተዳር ማዕረግ የዲላ ክስተር አስተባባሪና የውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር አክሊሉ አዳኝ ለተደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ዘጋቢ: አወል ከድር- ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
ብሔራዊ ምክክር ሀገራዊ አንድነትን ከማጠናከር ባሻገር ችግሮችን በውይይትና በሀሳብ የበላይነት ለመፍታት መሠረት እንደሚጥል ተገለጸ
የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2019 ጠቋሚ ዕቅድ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየመከረ ነው
የጠምባሮ ልዩ ወረዳ አርሶ አደሮች የመኸር እርሻ የማሳ ዝግጅት ቢያደርጉም በቂ ግብዓት አለማግኘታቸውን ገለጹ