የኢፌዲሪ ቱሪዝም ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በመሬት ናዳ ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የ3ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረጉ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 26/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢፌዲሪ ቱሪዝም ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በመሬት ናዳ ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የ3ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርገዋል።
የኢፌዲሪ ቱሪዝም ሚንስቴር ሚንስትር አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ በአደጋው ሳቢያ ለተጎዱ ወገኖች የተሰማቸውን ልባዊ ሐዘንም በዚህ ወቅት ገልጸዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ር/መስተዳር ማዕረግ የዲላ ክስተር አስተባባሪና የውሃ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር አክሊሉ አዳኝ ለተደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ዘጋቢ: አወል ከድር- ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
ለ7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ዞናዊ የብልጽግና ፓርቲ ማኒፌስቶ እና የምርጫ መወዳደሪያ ምልክት የማስተዋወቂያ መርሐ ግብር በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ይገኛል
በተቀናጀ የሕብረተሰብ ተሳትፎ የወባ ስርጭት መቆጣጠር መቻሉን በጋሞ ዞን የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ገለጸ
ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያን የብልፅግና ተምሳሌት የሚያደርጉ በርካታ ሥራዎች መከናወናቸው ተገለጸ