ዓመታዊ የቅዱስ ገብርኤል የንግስ በዓል በሀዋሳ ከተማ በድምቀት ተከበረ

ዓመታዊ የቅዱስ ገብርኤል የንግስ በዓል በሀዋሳ ከተማ በድምቀት ተከበረ

ሀዋሳ፡ ሐምሌ 19/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ዓመታዊው የቅዱስ ገብርኤል የንግስ በዓል በሲዳማ ክልል ሀዋሳ ከተማ በተለያዩ ሐይማኖታዊ ስርዓቶች በደምቀት ተከብሯል።

በዓመታዊ የንግስ በዓሉ ላይም ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ እንግዶች እንዲሁም የእምነቱ ተከታዮች ተሳትፈዋል፡፡

የንግሥ በዓሉ በየዓመቱ ሐምሌ 19 ቀን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ-ክርስቲያን ምዕመናን ዘንድ በድምቀት ይከበራል፡፡

ፎቶ፡ ሐና በቀለ