የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በተለያዩ የትምርህት መስክ ያሰለጠናቸውን ለ16ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ
በምርቃት መርሃ ግብር ላይ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ዶክተር ጉቼ ጉሌ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጡት ፕሮፌሰር ገብረ ያንትሱ : የወላይታ ሶዶ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ፎላ ከፍተኛ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች እና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ እና በተከታታይ የትምህርት መርሃ ግብር በተለያዩ የቅድመ እና ድህረ ምረቃ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ 859 ተማሪዎችን አስመረቀ ።
ተማሪዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን የመውጫ ፈተና ወስደው ውጤት አምጥተው መመረቃቸውን የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ዶክተር ጉቼ ጉሌ የተናገሩ ሲሆን በሀገር ደረጃ ለሰላም መስራት እንደሚገባ አመላክተዋል።
ተመራቂዎች ከዩኒቨርስቲ ያገኙት እውቀት በመጠቀም የተሻለ አገር ለመገንባት የሚደረገው ጥረት እንዲያግዙ ጥሪ ያቀረቡት የዕለቱ የክብር እንግዳ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ፕሮፌሰር ገብረ ያንትሱ ናቸው። የኢትዮጵያ የተፈጥሮ ጸጋ በመጠቀም ወደ ተሻለ ኑሮ ህዝብን ማሻገር ይገባል ብለዋል።
ዘጋቢ :- ፋሲል ሀይሉ

More Stories
በቡና ዘርፍ ያለውን ህገወጥ ንግድ በጋራ መግታት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የቡና ማህበር ገለጸ
6ኛው ሀገር አቀፍ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ የሰላም ኮንፍረንስ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ በተለያዩ ዝግጅቶች በአብዮ ኤርሳሞ መታሰቢያ ስታዲየም እየተካሄደ ነው
የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች መንግስት በከተማና በገጠር ለጀመራቸው የልማት እንቅስቃሴዎች ዋነኛ ሞተሮች ናቸው – አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር)