ሀዋሳ፡ ሰኔ 24/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የአርባ ምንጭ ቅርንጫፍ ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ለሚዲያ ባለሙያዎች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና እየሰጠ ነው።
የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጉጃ ጉሜ በዚህ ወቅት እንዳሉት ወደ ተቋሙ አዲስ የተቀላቀሉና ነባር ባለሙያዎች ወቅታዊ የሙያ ነክ ስልጠናዎችን በመውሰድ በዕውቀት እና በክህሎት የዳበሩ እንዲሆኑ አሳስበዋል።
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተግባቦት መመምህር ዕጩ ዶ/ር ተስፋዬ አለማየሁ በበኩላቸው የሚድያ ዘርፉ ተለዋዋጭ እና እያደገ በመጣው ዓለም ልክ ባለሙያውም ራሱን በተሻለ ዕውቀት እና መረጃ የታጠቀ መሆን እንዳለበት መክረዋል።
ትክክለኛ እና ወቅታዊ እንዲሁም ሚዛናዊ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ ለማድረስ በሚዲያ ዘርፉ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶችን ለማለፍ ተሽሎ መገኘት ይጠይቃል ያሉት ዕጩ ዶ/ር ተስፋዬ ሚዲያዎች ከቴክኖሎጂ ጋር መጓዝ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
ስፖርተኞች መልካም ስብእና ተላብሰው ውድድራቸውን እያካሄዱ እንደሚገኙ የጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ አስታወቀ
የፀረ-ተህዋስያን መድኃኒቶች በጀርሞች መላመድን ለመከላከል በሚደረገው አገራዊ ጥረት ውስጥ የሚዲያ ባለሙያዎች ግንባር ቀደም ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
መምህራን የሚገባቸውን ጥቅማ ጥቅምና መብት በማስጠበቅ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበር አስታወቀ