ሀዋሳ፡ ሰኔ 24/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የአርባ ምንጭ ቅርንጫፍ ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ለሚዲያ ባለሙያዎች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና እየሰጠ ነው።
የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጉጃ ጉሜ በዚህ ወቅት እንዳሉት ወደ ተቋሙ አዲስ የተቀላቀሉና ነባር ባለሙያዎች ወቅታዊ የሙያ ነክ ስልጠናዎችን በመውሰድ በዕውቀት እና በክህሎት የዳበሩ እንዲሆኑ አሳስበዋል።
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተግባቦት መመምህር ዕጩ ዶ/ር ተስፋዬ አለማየሁ በበኩላቸው የሚድያ ዘርፉ ተለዋዋጭ እና እያደገ በመጣው ዓለም ልክ ባለሙያውም ራሱን በተሻለ ዕውቀት እና መረጃ የታጠቀ መሆን እንዳለበት መክረዋል።
ትክክለኛ እና ወቅታዊ እንዲሁም ሚዛናዊ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ ለማድረስ በሚዲያ ዘርፉ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶችን ለማለፍ ተሽሎ መገኘት ይጠይቃል ያሉት ዕጩ ዶ/ር ተስፋዬ ሚዲያዎች ከቴክኖሎጂ ጋር መጓዝ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ