ሀዋሳ፡ ሰኔ 24/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የአርባ ምንጭ ቅርንጫፍ ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ለሚዲያ ባለሙያዎች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና እየሰጠ ነው።
የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጉጃ ጉሜ በዚህ ወቅት እንዳሉት ወደ ተቋሙ አዲስ የተቀላቀሉና ነባር ባለሙያዎች ወቅታዊ የሙያ ነክ ስልጠናዎችን በመውሰድ በዕውቀት እና በክህሎት የዳበሩ እንዲሆኑ አሳስበዋል።
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተግባቦት መመምህር ዕጩ ዶ/ር ተስፋዬ አለማየሁ በበኩላቸው የሚድያ ዘርፉ ተለዋዋጭ እና እያደገ በመጣው ዓለም ልክ ባለሙያውም ራሱን በተሻለ ዕውቀት እና መረጃ የታጠቀ መሆን እንዳለበት መክረዋል።
ትክክለኛ እና ወቅታዊ እንዲሁም ሚዛናዊ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ ለማድረስ በሚዲያ ዘርፉ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶችን ለማለፍ ተሽሎ መገኘት ይጠይቃል ያሉት ዕጩ ዶ/ር ተስፋዬ ሚዲያዎች ከቴክኖሎጂ ጋር መጓዝ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለምንም የፀጥታ ችግር መጠናቀቁን ተከትሎ የምስጋናና የዕውቅና መርሃ-ግብር ተካሄደ
የአካባቢ ብክለትን እና የካርበን ልቀትን ከመከላከል ባሻገር ለታዳሽ ሀይል ትኩረት ሊደረግ ይገባል – የክልሉ አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን
በዩኒቨርሲቲው በምርምር እና በቴክኖሎጂ ሽግግር ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት ከጊዜ ወደ ጊዜ ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸው ተገለፀ