የሴቶችን ግንዛቤ በማሳደግ ከተረጅነት ወደ ምርተማነት በማምራት ከዕዳ ወደ ምንዳ መሸጋገር እንደሚገባ የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ ገለጸ
“በጎነት ለእህትማማችነት፣ ለትውልድ ግንባታ እና ለዘላቂ ልማት” በሚል መሪ ቃል የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መድረክ በአርባምንጭ ከተማ ተካሂዷል ።
በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት እንደ ሀገር የተያዙ ዕቅዶች መኖራቸውን የተናገሩት በብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ሊግ ምክትል ፕሬዚዳንት ወ/ሮ መስከረም አበበ ዕቅዱን ከማሳካት አንፃር በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ዜጎችን ከተረጅነት አስተሳሰብ በማላቀቅ የሀገር ብልጽግናን ማረጋገጥ እንደሚገባ በብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ሊግ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ መዓዛ ካመቶ ገልጸዋል።
በብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ሊግ ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ዘሀራ ዑመድ ሴቶችን በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ እና በፖለቲካዊ ዘርፎች ይበልጥ ተሳታፊና ተጠቃሚ በማድረግ ሁሉ አቀፍ ለውጥ ማምጣት እንደሚገባ አሳስበዋል ።
በብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት በሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ሃላፊ አቶ መለሰ አለሙ በበኩላቸው የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ቀጣይነት ያለው ለውጥ ማምጣት እንደሚገባ ገልፀዋል ።
የመድረኩ ተሳታፊዎችም የሴቶችን ውሳኔ ሰጪነት አቅም ማጎልበት ይገባል ብለዋል ።
ዘጋቢ ፡ ሰለሞን አላሶ- ከአርባምንጭ ጣቢያችን
More Stories
በካፋ ዞን ጨና ወረዳ በምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም (FSRP) የተከናወኑ የልማት ስራዎች ላይ ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ጋር የልምድ ልውውጥ ተደረገ
ሳታ ቴክኖሎጂ እና ቢዝነስ ኮሌጅ በአርባ ምንጭ ካምፓስ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች በመጀመሪያ ዲግሪ እና ቴክኒክና ሙያ ስልጠና መስኮች ያሰለጠናቸውን 2 ሺህ 132 ተማሪዎችን አስመረቀ
በዕቅድ የሚመራ የመፈፀም አቅሙ ያደገ ሲቪል ሰርቫንት ለመገንባት እየተሰራ መሆኑን በደቡብ ኦሞ ዞን የሳላማጎ ወረዳ ሲቪል ሰርቪስ ጽ/ቤት ገለፀ