የሴቶችን ግንዛቤ በማሳደግ ከተረጅነት ወደ ምርተማነት በማምራት ከዕዳ ወደ ምንዳ መሸጋገር እንደሚገባ የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ ገለጸ
“በጎነት ለእህትማማችነት፣ ለትውልድ ግንባታ እና ለዘላቂ ልማት” በሚል መሪ ቃል የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መድረክ በአርባምንጭ ከተማ ተካሂዷል ።
በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት እንደ ሀገር የተያዙ ዕቅዶች መኖራቸውን የተናገሩት በብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ሊግ ምክትል ፕሬዚዳንት ወ/ሮ መስከረም አበበ ዕቅዱን ከማሳካት አንፃር በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ዜጎችን ከተረጅነት አስተሳሰብ በማላቀቅ የሀገር ብልጽግናን ማረጋገጥ እንደሚገባ በብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ሊግ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ መዓዛ ካመቶ ገልጸዋል።
በብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ሊግ ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ዘሀራ ዑመድ ሴቶችን በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ እና በፖለቲካዊ ዘርፎች ይበልጥ ተሳታፊና ተጠቃሚ በማድረግ ሁሉ አቀፍ ለውጥ ማምጣት እንደሚገባ አሳስበዋል ።
በብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት በሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ሃላፊ አቶ መለሰ አለሙ በበኩላቸው የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ቀጣይነት ያለው ለውጥ ማምጣት እንደሚገባ ገልፀዋል ።
የመድረኩ ተሳታፊዎችም የሴቶችን ውሳኔ ሰጪነት አቅም ማጎልበት ይገባል ብለዋል ።
ዘጋቢ ፡ ሰለሞን አላሶ- ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር የምርጥ ዘር ብዜት ስራን በራስ አቅም ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምርጥ ዘር ድርጅት አስታወቀ
በበልግ አዝመራ ከሚከናወኑ የግብርና ስራዎች ከ70 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት ታቅዷል – አቶ ማስረሻ በላቸው
የመንግሥትን የልማት ክፍተቶችን ለመሙላት የሚሰሩ የማህበረሰብ ልማት ድርጅቶች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት በተሻለ ለማረጋገጥ በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል – አምባሳደር ፍጹም አረጋ