የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ እውን ለማድረግ ጤናማ ማህበረሰብ መፍጠር እንደሚገባ ተገለጸ
ሀዋሳ፤ ግንቦት 01/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በአሪ ዞን የጂንካ ከተማ አስተዳደር “የማህበረሰብ መሪነት ለላቀ የኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከል” በሚል መሪ ቃል የኤች አይ ቪ ኤድስ ንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የጂንካ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በላይ ወልደ እንደተናገሩት፤ በሀገር አቀፍ ብሎም በከተማ አስተዳደሩ የተጀመረውን የብልጽግ እውን ለማድረግ ጤናማ ማህበረሰብ መፍጠር ይገባል።
በበጀት አመቱ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ተቋሙ በርካታ አመርቂ የጤና ተግባራት ማከናወኑን አመላክተው በቀጣይ ተቋሙ የኤች አይ ቪ ኤድስን መከላከልና መቆጣጠርን ጨምሮ በንቅናቄና በዘመቻ የጤና ተግባራት ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።
በአሪ ዞን የጂንካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አስፋው ዶሪ በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት ጤና ለሁሉም ተግባር መሠረት ቢሆንም በከተማ አስተዳደሩ አምራቹን የማህበረሰብ ክፍል በከፍተኛ ሁኔታ እያጠቃ ያለውን የኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና የመቆጣጠር ሥራው እየተዘናጋ ነው ብለዋል።
በቀጣይ የጤና ሥራን ጨምሮ ከተማ አስተዳደሩ በ100 ቀናት ዕቅድ በሚያከናውናቸው ተግባራት የኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ትኩረት ተሰጥቶበት ይሰራል ብለዋል።
ከተማ አስተዳደሩ በቀጣይ 100 ቀናት ለሚያከናውናቸው ሁሉ አቀፍ ተግባራት ስከታማነት ተቋማትና ግለሰቦች የድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።
በመድረኩ የኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠርን ጨምሮ የተቋሙ የ9 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ቀርቦ ውይይት ተደርጓል።
ዘጋቢ፡ መልካሙ ቡርዝዳቦ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የታላቁ ህዳሴ ግድብን እንዳጠናቀቅን ሁሉ የባህር በርን ለማስመለስ የሚደረገውን ጥረት በይበልጥ ማገዝ እና መደገፍ እንደሚገባ ተጠቆመ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፋይናንስ ቢሮ ከፌደራል ገንዘብ ሚኒስቴር እና ከክልሉ አመራር አካዳሚ ጋር በመተባበር በመንግስት ፋይናንስ አስተዳደር ዙሪያ ለኦዲት ባለሙያዎች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል
ህገወጥ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ