“እናንተ ባበረከታችሁት አስትዋፅኦ የሰላምና የልማት ሥራዎችን እየሰራን በመሆኑ በክልሉ ስም ምስጋና ይገባችኃል” – አቶ እንዳሻው ጣሰው
ሀዋሳ: ሚያዝያ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው በክልሉ የሚገኙ ግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች ላበረከቱት አስተዋጽዖ ምስጋና አቅርበዋል::
ርእሰ መስተዳድሩ በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል “ግብር ለሀገር ክብር” በሚል መሪ ቃል ክልላዊ የታክስ ህግ ተገዥነት የንቅናቄ እና የግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች የእውቅናና ሽልማት መርሀግብር ላይ ተገኝተው ለታማኝ ግብር ከፋዮች ምስጋና አቅርበዋል::
“ታማኝ ሆናችሁ ባበረከታችሁት አስተዋፅፆ የሰላም የልማት ሥራዎችን እየሰራን በመሆኑ በክልሉ ስም ምስጋና ይገባችኃል” ነው ያሉት ርእሰ መስትዳድሩ::
በዘርፉ ያሉ የገቢ ሠራተኞችም አድልኦ የሌለበት ፍትሀዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡ ያሳሰቡ ሲሆን በቀጣይም ለኢትዮጵያ ብልፅግና ተግተን በጋራ እንሠራለን ብለዋል ርእሰ መስተዳድሩ::
በመርሀ ግብሩ ላይ ግብርን በታማኝነት በመክፈል የዜግነት ግዴታቸውን መወጣት የቻሉ ግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች እውቅናና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል::
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ
More Stories
በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በቋሚነት የሚደገፉበት ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የቡርጂ ዞን አስተዳደር አስታወቀ
“አንድ ሰው ወደዚህች ምድር ሲመጣ እንዲሰራ የተፈቀደለትና የሚጠበቅበት ነገር አለ” – ታደሰ ገብሬ /ጃክሰን/
በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ጉልህ ድርሻ እንዳለው ተገለጸ