“እናንተ ባበረከታችሁት አስትዋፅኦ የሰላምና የልማት ሥራዎችን እየሰራን በመሆኑ በክልሉ ስም ምስጋና ይገባችኃል” – አቶ እንዳሻው ጣሰው
ሀዋሳ: ሚያዝያ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው በክልሉ የሚገኙ ግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች ላበረከቱት አስተዋጽዖ ምስጋና አቅርበዋል::
ርእሰ መስተዳድሩ በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል “ግብር ለሀገር ክብር” በሚል መሪ ቃል ክልላዊ የታክስ ህግ ተገዥነት የንቅናቄ እና የግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች የእውቅናና ሽልማት መርሀግብር ላይ ተገኝተው ለታማኝ ግብር ከፋዮች ምስጋና አቅርበዋል::
“ታማኝ ሆናችሁ ባበረከታችሁት አስተዋፅፆ የሰላም የልማት ሥራዎችን እየሰራን በመሆኑ በክልሉ ስም ምስጋና ይገባችኃል” ነው ያሉት ርእሰ መስትዳድሩ::
በዘርፉ ያሉ የገቢ ሠራተኞችም አድልኦ የሌለበት ፍትሀዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡ ያሳሰቡ ሲሆን በቀጣይም ለኢትዮጵያ ብልፅግና ተግተን በጋራ እንሠራለን ብለዋል ርእሰ መስተዳድሩ::
በመርሀ ግብሩ ላይ ግብርን በታማኝነት በመክፈል የዜግነት ግዴታቸውን መወጣት የቻሉ ግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች እውቅናና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል::
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ
More Stories
“አንድነታችንን በማጎልበት የህዝብ ጥቅም የሚያስቀድም ፖለቲካ ማራመድ ይጠበቅብናል” ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
የሕብረ-ብሔራዊ አንድነት መጠናከር መሰረት የሆነው ብዝሃነትን በአግባቡ የማስተናገድ ሂደት ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያለው መሆኑ ተገለፀ
በክረምቱ ወራት ሊከሰቱ የሚችሉ የተለያዩ አደጋዎችን ለመከላከል አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ