“እናንተ ባበረከታችሁት አስትዋፅኦ የሰላምና የልማት ሥራዎችን እየሰራን በመሆኑ በክልሉ ስም ምስጋና ይገባችኃል” – አቶ እንዳሻው ጣሰው
ሀዋሳ: ሚያዝያ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው በክልሉ የሚገኙ ግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች ላበረከቱት አስተዋጽዖ ምስጋና አቅርበዋል::
ርእሰ መስተዳድሩ በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል “ግብር ለሀገር ክብር” በሚል መሪ ቃል ክልላዊ የታክስ ህግ ተገዥነት የንቅናቄ እና የግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች የእውቅናና ሽልማት መርሀግብር ላይ ተገኝተው ለታማኝ ግብር ከፋዮች ምስጋና አቅርበዋል::
“ታማኝ ሆናችሁ ባበረከታችሁት አስተዋፅፆ የሰላም የልማት ሥራዎችን እየሰራን በመሆኑ በክልሉ ስም ምስጋና ይገባችኃል” ነው ያሉት ርእሰ መስትዳድሩ::
በዘርፉ ያሉ የገቢ ሠራተኞችም አድልኦ የሌለበት ፍትሀዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡ ያሳሰቡ ሲሆን በቀጣይም ለኢትዮጵያ ብልፅግና ተግተን በጋራ እንሠራለን ብለዋል ርእሰ መስተዳድሩ::
በመርሀ ግብሩ ላይ ግብርን በታማኝነት በመክፈል የዜግነት ግዴታቸውን መወጣት የቻሉ ግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች እውቅናና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል::
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ
More Stories
አርብቶ አደሩን ከእንስሳት ሀብት ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ ደረጃቸውን የጠበቁ ዘመናዊ የእንስሳት ኤክስፖርት ማዕከላት እንደሚያስፈልጉ ተጠቆመ
በጌዴኦ ዞን የጤና መድህን አባል የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን የይርጋ ጨፌ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽህፈት ቤት አስታወቀ
ሃኪም ዚዬች ወደ ዋይዳድ ካዛብላንካ ለመዛወር ተስማማ