“እናንተ ባበረከታችሁት አስትዋፅኦ የሰላምና የልማት ሥራዎችን እየሰራን በመሆኑ በክልሉ ስም ምስጋና ይገባችኃል” – አቶ እንዳሻው ጣሰው
ሀዋሳ: ሚያዝያ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው በክልሉ የሚገኙ ግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች ላበረከቱት አስተዋጽዖ ምስጋና አቅርበዋል::
ርእሰ መስተዳድሩ በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል “ግብር ለሀገር ክብር” በሚል መሪ ቃል ክልላዊ የታክስ ህግ ተገዥነት የንቅናቄ እና የግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች የእውቅናና ሽልማት መርሀግብር ላይ ተገኝተው ለታማኝ ግብር ከፋዮች ምስጋና አቅርበዋል::
“ታማኝ ሆናችሁ ባበረከታችሁት አስተዋፅፆ የሰላም የልማት ሥራዎችን እየሰራን በመሆኑ በክልሉ ስም ምስጋና ይገባችኃል” ነው ያሉት ርእሰ መስትዳድሩ::
በዘርፉ ያሉ የገቢ ሠራተኞችም አድልኦ የሌለበት ፍትሀዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡ ያሳሰቡ ሲሆን በቀጣይም ለኢትዮጵያ ብልፅግና ተግተን በጋራ እንሠራለን ብለዋል ርእሰ መስተዳድሩ::
በመርሀ ግብሩ ላይ ግብርን በታማኝነት በመክፈል የዜግነት ግዴታቸውን መወጣት የቻሉ ግንባር ቀደም ግብር ከፋዮች እውቅናና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል::
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ

More Stories
በዶሮ እርባታ ዘርፍ በመሰማራት የተሻለ ውጤት እያስመዘገቡ መሆናቸውን የየም ዞን ሣጃ ከተማ በዘርፉ የተሰማሩ ሰዎች ተናገሩ
የከተማውን መሰረተ ልማት ከማሟላት ባሻገር ለነዋሪዎች ምቹ እና ማራኪ በማድረግ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
የዱራሜ ከተማ የኮሪደር ልማት ሥራ በአዲስ መልክ በዘመናዊ ዲዛይን እየተሰራ መሆኑን የዱራሜ ከተማ አስተዳደር ገለፀ