በማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ፣ የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ፣ የማዕድን ሚኒስትር ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኝን ጨምሮ የክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊዎችና ሌሎች የዘርፉ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
የግብርና ሚኒስትሩ ዶክተር ግርማ አመንቴ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት በአገሪቱ ከሚታረሰው ማሳ 43 በመቶ ማለትም 7 ሚሊየን ሄክታር መሬት በአሲዳማነት የተጠቃ ነው።
በ2016/17 ምርት ዘመን 100 ሺህ ሄክታር መሬት በኖራ ለማከም ታቅዶ እየተሠራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
ለዚህም 1.5 ቢሊየን ብር ከመንግሥትና ከልማት አጋሮች እንደሚያስፈልግ የግብርና ሚኒስትሩ አመላክተዋል።
የግብርና ኖራ አቅርቦትና ስርጭት ማስፈጸሚያ ሰነድ በኢንቨስትመንትና የግብአት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ በሆኑት በዶክተር ሶፊያ ካሳ ቀርቧል።
ሰነዱን መነሻ በማድረግ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ መሪነት ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ፡ ጌታሁን አንጭሶ
More Stories
የሆሳዕና ወርልድ ብራይት ኮሌጅ ለ6ኛ ዙር በድፕሎማ፣በመጀመሪያ ድግሪና በሁለተኛ ድግሪ በተለያዩ የስልጠና መርሃ ግብሮች ያሰለጠናቸውን 2ሺ783 ተማሪዎችን እያስመረቀ ነው
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በጎፋ ዞን በመሬት መንሸራተት ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች በስፍራው ተገኝተው አፅናኑ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ከንቾ ሻቻ ጎዚዲ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት መንሽራት አደጋ ምክንያት ህይወታቸውን ያጡ ወገኖቻችንን በማሰብ ከሐምሌ 20/2016 ዓ.ም ጀምሮ ለ3 ተከታታይ ቀናት ብሔራዊ የሀዘን ቀን ታውጇል