በማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ፣ የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ፣ የማዕድን ሚኒስትር ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኝን ጨምሮ የክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊዎችና ሌሎች የዘርፉ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
የግብርና ሚኒስትሩ ዶክተር ግርማ አመንቴ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት በአገሪቱ ከሚታረሰው ማሳ 43 በመቶ ማለትም 7 ሚሊየን ሄክታር መሬት በአሲዳማነት የተጠቃ ነው።
በ2016/17 ምርት ዘመን 100 ሺህ ሄክታር መሬት በኖራ ለማከም ታቅዶ እየተሠራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
ለዚህም 1.5 ቢሊየን ብር ከመንግሥትና ከልማት አጋሮች እንደሚያስፈልግ የግብርና ሚኒስትሩ አመላክተዋል።
የግብርና ኖራ አቅርቦትና ስርጭት ማስፈጸሚያ ሰነድ በኢንቨስትመንትና የግብአት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ በሆኑት በዶክተር ሶፊያ ካሳ ቀርቧል።
ሰነዱን መነሻ በማድረግ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ መሪነት ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ፡ ጌታሁን አንጭሶ

More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ 25 ሺህ 338 ሊትር ቤንዝልና 62 ሺ 686 ሊትር ናፍጣ በቁጥጥር ስር መዋሉን የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ አስታወቀ
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ