የጎፋ ዞን የሕዝብ እንደራሴዎች የመራጭ ተመራጭ መድረክ አካሄዱ
ሀዋሳ፡ የካቲት 21/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጎፋ ዞን በዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ ምርጫ ክልል በበቶ ከተማ አስተዳደር የፌዴራል እና የክልል ተመራጮች ከመረጣቸው ሕዝብ ጋር ውይይት አካሂደዋል።
በመድረኩም የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች፣ የሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች፣ የተጀመሩ የፌደራልና የክልል ፕሮጀክቶች ወቅቱን ጠብቀው በመጠናቀቅ ለህዝቡ ጥቅም መስጠት እንዳለባቸው፣ የአከባቢውን የመሬትና የመልማት እምቅ አቅም ለመጠቀም በስፋት ቴክኖሎጂን በመጠቀም ማምረት እንዳለባቸው የኤፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አቶ ጋሻያለው ጋለ አሳስበዋል።
በተጨማሪም በውይይቱ በበጀት ዓመቱ በስድስት ወር በተሰሩና ቀጣይ በሚሰሩ ተግባራት ማለትም በሰላምና በፀጥታ ሥራዎች፣ በኢኮኖሚ ጉዳዮች፣ በማህበራዊና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ተደርጓል።
በመጨረሻም የህዝብ ተመራጮቹ ከህዝቡ ለተነሱ ጥያቄዎችና የልማት ፍላጎቶች ምላሽና ቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል።
ምንጭ ፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት

More Stories
የምሁራን አንድነትን ማጠናከርና የእርስ በእርስ መከባበር ባህልን ማጎልበት ለአካባቢው ዘላቂ ሠላም መስፈን ወሳኝነት እንዳለው ተመላከተ
በብልጽግና ፓርቲ የሥራ አስተባባሪዎችና ዕጩ ወኪሎች ኃላፊነትና ግዴታ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ
የመምህራንን ኑሮ ለማሻሻል እና ሙያዊ ክብራቸውን ለመመለስ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን በቤንች ሸኮ ዞን የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር ሰለሞን ለዊ ተናገሩ