የጎፋ ዞን የሕዝብ እንደራሴዎች የመራጭ ተመራጭ መድረክ አካሄዱ
ሀዋሳ፡ የካቲት 21/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጎፋ ዞን በዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ ምርጫ ክልል በበቶ ከተማ አስተዳደር የፌዴራል እና የክልል ተመራጮች ከመረጣቸው ሕዝብ ጋር ውይይት አካሂደዋል።
በመድረኩም የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች፣ የሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች፣ የተጀመሩ የፌደራልና የክልል ፕሮጀክቶች ወቅቱን ጠብቀው በመጠናቀቅ ለህዝቡ ጥቅም መስጠት እንዳለባቸው፣ የአከባቢውን የመሬትና የመልማት እምቅ አቅም ለመጠቀም በስፋት ቴክኖሎጂን በመጠቀም ማምረት እንዳለባቸው የኤፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አቶ ጋሻያለው ጋለ አሳስበዋል።
በተጨማሪም በውይይቱ በበጀት ዓመቱ በስድስት ወር በተሰሩና ቀጣይ በሚሰሩ ተግባራት ማለትም በሰላምና በፀጥታ ሥራዎች፣ በኢኮኖሚ ጉዳዮች፣ በማህበራዊና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ተደርጓል።
በመጨረሻም የህዝብ ተመራጮቹ ከህዝቡ ለተነሱ ጥያቄዎችና የልማት ፍላጎቶች ምላሽና ቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል።
ምንጭ ፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት

More Stories
በዶሮ እርባታ ዘርፍ በመሰማራት የተሻለ ውጤት እያስመዘገቡ መሆናቸውን የየም ዞን ሣጃ ከተማ በዘርፉ የተሰማሩ ሰዎች ተናገሩ
የከተማውን መሰረተ ልማት ከማሟላት ባሻገር ለነዋሪዎች ምቹ እና ማራኪ በማድረግ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
የዱራሜ ከተማ የኮሪደር ልማት ሥራ በአዲስ መልክ በዘመናዊ ዲዛይን እየተሰራ መሆኑን የዱራሜ ከተማ አስተዳደር ገለፀ