የጎፋ ዞን የሕዝብ እንደራሴዎች የመራጭ ተመራጭ መድረክ አካሄዱ
ሀዋሳ፡ የካቲት 21/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጎፋ ዞን በዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ ምርጫ ክልል በበቶ ከተማ አስተዳደር የፌዴራል እና የክልል ተመራጮች ከመረጣቸው ሕዝብ ጋር ውይይት አካሂደዋል።
በመድረኩም የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች፣ የሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች፣ የተጀመሩ የፌደራልና የክልል ፕሮጀክቶች ወቅቱን ጠብቀው በመጠናቀቅ ለህዝቡ ጥቅም መስጠት እንዳለባቸው፣ የአከባቢውን የመሬትና የመልማት እምቅ አቅም ለመጠቀም በስፋት ቴክኖሎጂን በመጠቀም ማምረት እንዳለባቸው የኤፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አቶ ጋሻያለው ጋለ አሳስበዋል።
በተጨማሪም በውይይቱ በበጀት ዓመቱ በስድስት ወር በተሰሩና ቀጣይ በሚሰሩ ተግባራት ማለትም በሰላምና በፀጥታ ሥራዎች፣ በኢኮኖሚ ጉዳዮች፣ በማህበራዊና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ተደርጓል።
በመጨረሻም የህዝብ ተመራጮቹ ከህዝቡ ለተነሱ ጥያቄዎችና የልማት ፍላጎቶች ምላሽና ቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል።
ምንጭ ፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት
More Stories
በሁሉም ዘርፍ የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የሴቶች የልማት ህብረትንና የስትሪንግ ኮሚቴ እንቅስቃሴን ይበልጥ ሊጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ
የሴቶች የልማት ህብረትን በማጠናከር የሴቶችን ተጠቃሚነት በይበልጥ ማረጋገጥ ይገባል – ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
በዞኑ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በግብርናው ዘርፍ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እንደሚሰራ የጋሞ ዞን አሰተዳደር አሰታወቀ